| Journalist Eskinder Nega |
ኢሳት ዜና:-በሽብር ወንጀል ተከሶ 18 ዓመታት የግፍ እስር የተፈረደበት ታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ዛሬ
ረፋዱ ላይ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ለማቅረብ ተገኝቶ ነበር። እስክንድር ይግባኝ ለማለት ዝግጅቱን ያጠናቀቀ
ቢሆንም፣ የይግባኙን ሰነድና ለፍርድ ቤት ሊያቀርበው ያዘጋጀውን የወረቀት ማስታወሺያዎች የቃሊቲ እስር ቤት ፖሊሶች
ስለነጠቁት ሳይችል ቀርቷል።
ጋዜጠኛ እስክንድር ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ለእስር ቤት ፖሊሶች ትእዛዝ እንዲጻፍለትና አጭር ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።
