Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Wednesday, August 29, 2012

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በልዩ ትእዛዝ ተፈታ::

ኢሳት ዜና:- ማክሰኞ ነሐሴ 22 ቀን 2004 ዓ.ም፡- የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፍትህ ሚኒስትር ፕሬዝዳንት ልዩ ትዕዛዝ በፌዴራል ዐቃቤ ህግ የቀረበበት ክስ ተቋርጦ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንዲፈታ በተወሰነው መሰረት ዛሬ ከቀኑ 8 ሰአት ላይ ተፈትቷል።

ምንጮቻችን እንደገለጹልን በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 16ተኛ ወንጀል ችሎት በዐቃቤ ህግ የቀረበበት ክስ የጋዜጠኛውን የዋስትና መብት የማያስነፍገው ሆኖ ሳለ ዐቃቤ ህግ በማረሚያ ቤት ሆኖ ክሱን ይከራከርልኝ ስላለ ብቻ የችሎቱ ዳኛ ማጽደቃቸው እና የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ መታሰር፣ እንዲሁም በዕለቱ ችሎት የገዢው ፓርቲ ደጋፊ የሆነው የኢትዮ ቻናል ጋዜጣ ባለቤት ሳምሶም ማሞ እና የትዳር አጋሩ የተከሰሱበት የንግድ ፈቃድ ሳያድሱ የመስራት ወንጀል በፍትህ ሚንስትር ዲኤታ ውሳኔ ክሱ እንዲቋረጥ ተደርጎ መሰናበቱ የፍትህ ሥርዓቱን በሀገር ዓቀፍና በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ያጋለጠና ያሳጣ ጉዳይ ሆኖ በመንግሥት ላይ ኪሳራ አምጥቷል፡፡

አባይን የደፈረ መሪ የሚል ፎቶ ግራፍ እያዞሩ የሚሸጡ የጎዳና ላይ ነጋዴዎች በፖሊስ እየተዋከቡ ነው::

ኢሳት ዜና:- ነሀሴ ፳፪ (ሀያ ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
የአቶ መለስ ዜናዊን ከዚህ አለም በሞት መለየት ተከትሎ፣ መንግስት በይፋ በየከተማው ሙሾ እአስወረደ በሚገኝበት በዚህ ወቅት፣ የአዲስ አበባ ፖሊሶች  “አባይን የደፈረው መሪ” የሚል ጽሁፍ ያለበትን የአቶ መለስ ዜናዊን ፎቶ ግራፍ በፒያሳ ጎዳናዎች ላይ ፣ በ5 ብር ሲሸጡ የተገኙ የጎዳና ላይ አዟሪዎች በፖሊስ ተይዘው የሚሸጡዋቸውን ፎቶዎች እንዲቀሙ ተደርጓል።

Tuesday, August 28, 2012

ከአቶ መለስ ሞት ጋር በተያያዘ በበርካታ ዜጎች ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተፈፀመ እንደሚገኝ ተገለፀ።

ኢሳት ዜና:- (Aug. 28) የአብዴፓ ፕሬዚዳንት ተደብድበዋል፤ የአንድነት ፓርቲ አባላትም እየታሰሩ ነው። በቂሊንጦ እስር ቤት፡የሚገኙት የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ ዘሪሁን ገብረ እግዚአብሔር፦“መለስ መሞታቸው በቴሌቪዥን በተነገረበት ጊዜ ሌሎቹ ሲያለቅሱ፤ አንተ ስቀሀል” ተብለው ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል።

ስብሐት ነጋ የቀድሞ የህወሓት አመራር አባላላትን እያደራጁ ነው

Ethioforum.org: አውራምባ ታይምስ (አዲስ አበባ) – የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ መስራችና የድርጅቱ የሞራልና የፍልስፍና አባት ተደርገው የሚወሰዱት አቶ ስብሐት ነጋ በ1993 ዓ.ም ክፍፍል ወቅት ከድርጅቱ የተሰናበቱ አባላትን አንድ በአንድ በማነጋገር ድርጅቱ በአዲስ መልክ ህልውናውን እንዲያጠናክር በማደራጀት ላይ እንደሚገኙ የአውራምባ ታይምስ አስተማማኝ ምንጮች ከአዲስ አበባ ገልጸዋል፡፡

‹‹መለስ እራሱን ብቻ ሳይሆን ሀወሓትንም ጭምር ገድሎ ነው የሞተው›› የሚሉት ስብሐት ነጋ ‹‹በትጥቅ ትግሉ ወቅት የጎላ ድርሻ የነበራቸውና ችግርና መከራን ተጋፍጠው ህወሓት ውስጥ በጽናት የዘለቁ አመራሮች ወደ ጎን ተገፍተው፤ ዛሬ ድርጅቱ የእነ አዜብ መፈንጫ ሆኗል›› ማለታቸውን ጠቅሰው ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ 

Monday, August 27, 2012

በመለስ ዜናዊ ሞት ደስታዋን የገለጸችው ወጣት በአደባባይ ተገደለች

ባሳለፍነው ሳምንት የህይወት እልፈታቸውን የሰማነው የህወሃት ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር እና የኢትዮጵያ የቁጭ በሉ ጠቅላይ ሚንስትር የሆኑትን የአቶ መለስ ዜናዊን ሞት አስመልክቶ ከፍተኛ እና ሳዛኝ ዜና ከሃገራችን የደረሰን ሲሆን በደጋፊዎች እና በተቃዋሚዎች መካከልም ከፍተኛ ቅራኔን እየፈጠረ ነው ። 

በተለይም  የጠቅላይ ሚንስትሩን ሞት የዜናን እወጃ ስመልክቶ እንኳን ሞተ ጨካኝ ነበር በማለት የውስጥ ፍላጎቷን በድንገተኛ ሰሜት የገለጸችውን ወጣት ከሜሪካ ለጉብኝት የሄደው የወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ እየተዝናኑ ባሉበት ካፍቴሪያ ውስጥ  በጠርሙስ ጭንቅላቷ ላይ በመምታት የገደላት መሆኑን ከስፍራው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል ።

ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ጠቅላይ ሚንስትሩን ተከትለው ሄደዋል መሞታቸው በአዲስ አበባ በስፋት እየተነገረ ነው።

ዘንድሮ ወያኔን እና ወያኔን አፍቃሪያን ምን ነካቸው ያሰኛል በከፍተኛ አመራሮች ላይ ክፉኛ የሞት ጥላ ጥላውን አድርቶባቸዋል።በዚህ ወር ብቻ ሶስት ታላላቅ ወያኔ እና ወያኔ አፍቃሪያንን በሞት ጥላ ተነጥቀናል። የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕረዚዳንት ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ከዚህ አለም በሞት ተለየ ፣በአዲስ አበባ በአሁን ሰአት በከፍተኛ ደረጃ እየተናፈሰ ያለው ወቅታዊ ወሬ ከመለስ ዜናዊ ሞት ባሻገር  የፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ መሞት እንደሆነ ተገልጾአል ። 

የ21 ዓመታት መከራን ያላገናዘበ የወ/ሮ አዜብ መስፍን መሪር ሀዘን፡ በፍቅሬ ዘለቀው (ኖርዎይ)


የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ም/ቤት ታማኝ ምንጮችን ጠቅሰው የአቶ መለስ ዜናዊን ዜና እረፍት ካወጁ እነሆ ከአርባ ቀናት በላይ አለፈው። ይሁን እንጂ አቶ በረከት ስምዖን የሚመሩት የኮምኒኬሽን ሚኒስቴር ቢሮ ሲያቀናብረውና ሲያሰራጨው ከነበረው የውሸት ድራማ፣ አይቀሬነቱ ደርሶ እነሆ በ15/12/04 ዓ.ም ውዥንብር ውስጥ ከተውት ለነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ይፋ ተደርጓል። ይህንንም ተከትሎ የአቶ መለስ ቤተሰቦች፣ ዘመዶች፣ ወዳጆች፣ ደጋፊዎችና የስርዓቱ ተጠቃሚዎች መሪር ሀዘናቸውን እየገለፁና በማስገደድ እያስለቀሱን ይገኛሉ።

የኢህአዲግ አጋር የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የክልል መስተዳድር አካላት፣ በአምሳላቸው ተጠፍጥፈው የተሰሩ የተለያዩ የሲቪክ ማህበራት ሐላፊዎች፣ የመንግስት ሠራተኞች፣ ታዋቂ ነጋዴዎች፣ ግለሰቦችና ከመቼውም በላይ በሥርዓቱ ተጠቂ የሆኑውን ብዙሀን ማሕበረሰብ በካድሬዎች እየተገደዱ፣ እንደ ጣዖት ለሚያመልኩት መሪያቸው ሕዝቡን በማስፈራራት በርሀብ በጠበሰ አንጀት እያስለቀሱና ድራማ እያሰሩት ይገኛሉ። እጅግ በጣም የሚገርመው ደግሞ የጎዳና ተዳዳሪዎች፣ ለማኞችና በሆስፒታል የተኙ በሽተኞች የመሪያችሁን ሀዘን ወጥታችሁ ግለፁ መባላቸው የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪሚል ሱንግ በሞተ ጊዜ ከተፈፀመው በከፋ ሁኔታ ከላይ ከመንግስት በወረደ ትዕዛዝ እምባ ለማውጣት ሲታገሉ ማየት የሚያሳፍርም የሚገርምም ነው።

Sunday, August 26, 2012

የአቶ ሀይለማርያም ጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ ኢህአዴግን እያወዛገበ ነው

ኢሳት ዜና:- ነሀሴ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ከአራት ቀናት በፊት የ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሞት ይፋ ባደረገበት ወቅት  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ፤አቶ መለስን ተክተው በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንደሚሰሩ መወሰኑን ይፋ ቢያደርግም፤ በተለይ በህወሀት በኩል በተቀሰቀሰ ከፍተኛ ተቃውሞ እስካሁን የአቶ ሀይለማርያም ሹመት ሊጸድቅላቸው እንዳልቻለ  የኢሳት የውስጥ ምንጮች ጠቁመዋል።

አቶ ሀይለማርያም ፤የአቶ መለስ አስከሬን ከብራሰልስ አዲስ አበባ የገባ ዕለት ምሽት  በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሢሰጡ፤ “መለስን መተካት ከባድ ነው” ማለታቸው ይታወሳል።

የኩማ አስተዳደር በይፋ ድንኳን ተክሎ ለቅሶ ተቀመጠ

ኢሳት ዜና:- ነሀሴ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
የኩማ አስተዳደር በተለምዶ ማዘጋጃ ቤት ተብሎ በሚጠራው ቅጥር ግቢ ውስጥ የጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊን  ሞት አስመልክቶ ሁለት ትልልቅ ድንኩዋኖችን በግቢው ውስጥ ተክሎአል።

አስተዳደሩ ከፌዴራል መንግስት በተለየ የከተማዋ ነዋሪዎች ሐዘናቸውን የሚገልጹበት ቦታ ያስፈልጋል በሚል ሁለት ትልልቅ ድንኩዋን ትላንት የተከለ ሲሆን አንዳንድ ሰዎች ሐዘናቸውን በለቅሶ በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እንዳይጎበኝ በበላይ አካል ተከልክሏል” ይላሉ የማረሚያ ቤት ምክትል ኃላፊ

ኢሳት ዜና:- ነሀሴ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ከትላንት በስተያ ዕለት በፌዴራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 16 ወንጀል ችሎት የዋስትና መብቱ ተገፎ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሆኖ ክሱን እንዲከላከል የተፈረደበት የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፌዴራል ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የታሰረበት ዞን /ቀጠና/ እና ክፍል አልታወቀም፤ ሊጎበኙት የመጡ ሰዎች ሁሉ እንዳያገኙት ተከልክለዋል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገንን ለመጠየቅ መጥተው አለ የተባለበት ቦታ ባለመገኘቱ እና የማረሚያ ቤቱ ሰራተኞች ሊያቀርቡላቸው ባለመቻላቸው  የተማረሩት የሙያ አጋሮቹ የማረሚያ ቤትን ምክትል ኃላፊን ሄደው ቢያነጋግሩም ኃላፊው “ የፍትህ ጋዜጣ ተመስገን ደሳለኝን ነው፣ በሉ እርሱን መቼም ልታገኙት አትችሉም፣ ይህ የበላይ አካል ውሳኔ ነው፤ ዝም ብላችሁ ምግቡን ብቻ ጥላችሁለት ሂዱ፣ እኛ እናደርሳለን” ብለዋል፡፡