| አቶ ቡልቻ ደመቅሳ |
ኢሳት ዜና:-“በቀጣይ በኢትዮጵያ የተሸለ ነገር የሚመጣው፤ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ ተገናኝተው፣ በክብ ጠረጴዛ
ዙሪያ ተመካክረው መፍትሔ ማምጣት የሚችሉበት ዕድል ሲፈጠር ብቻ ነው።” ሲሉ አቶ ቡልቻ ወደ ሥልጣን እየመጣ ላለው
አዲስ አመራር ቡድን መልዕክት አስተላለፈዋል።
የቀድሞው የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀ-መንበር ይህን ያሉት፤ዛሬ ለንባብ ከበቃው ሰንደቅ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ነው። “ከጠ/ሚኒስትር
መለስ ዜናዊ ሞት በኃላ አስተዳደሩን ከተረከበው አዲስ አመራር ምን ይጠበቃል?” በማለት ጋዜጣው ላቀረበላቸው
የመጀመሪያ ጥያቄ አቶ ቡልቻ ፦” አዲስ አመራር አለን’ንዴ?”በማለት ነበር ጥያቄውን በጥያቄ የመለሱት።



