| alamata |
ኢሳት ዜና:-በትግራይ ክልል በአለማጣ ወረዳ የሚኖሩ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ተቃውሞአቸውን እያሰሙ
ያሉት ፣ የወረዳው የቤት አፍራሽ ግብረሀይል አባላት በህገወጥ መንገድ ተስርተዋል ያሉዋቸውን ቤቶች ለማፍረስ
በሄዱበት ወቅት ነው።
ተማሪዎች፣ ህጻናት ፣ አዋቂዎች ከጧቱ 3 ሰአት ጀምሮ እስከ አመሻሹ ድረስ መንገዶችን በመዝጋት ተቃውሞአቸውን
የገለጡ ሲሆን፣ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ የሚተላለፉ መኪኖች መተላለፊያዎች ተዘግተውባቸው ውለዋል።