Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, August 4, 2012

ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ በኩዌት ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እራሷን አጠፋች

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
አረብ ታይምስ ትናንት ባወጣው ዘገባ እንደገለፀው ከሆነ፣ ኢትዮጵያዊቷ ትሰራበት የነበረው ቤት ውስጥ ራሷን የመግደል ሙከራ ስታደርግ ተይዛ ወደ ሆስፒታል ተወስዳ ስነልቦና ሕክምና እንድትወስድ ተደርጋ ነበር።

ሆኖም ከሆስፒታሉ ስትወጣ  “ጃሃራ” በሚባል ስፍራ ወደሚገኘው “አል-ነኢም” ፖሊስ ጣቢያ ተወስዳ በመታሰር በምርመራ ላይ ሳለች፤ የእስር ቤቱ መታጠቢያ ቤት ውስጥ አድርጋው በነበረው ሂጃብ  የራሷን ሕይወት አጥፍታ ተረኛው ፖሊስ እስረኞችን በሚጎበኝበት ወቅት አስከሬኗን ማግኘቱን ዘግቧል።

አረብ ታይምስ ሟቿ ኢትዮጵያዊ መሆኗን ከመግለጽ በቀር ስለማንነቷ የገለፀው ምንም አይነት መረጃ የለም።

No comments:

Post a Comment