Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, December 1, 2012

አዲሱ የስልጣን ክፍፍልና አመክንዮው: (በዳዊት ተሾመ)

 እንደ መግቢያ
ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረውን የካቢኒያቸውን ሽግሽግና አዲስ ተሿሚ ሚኒስትሮቻቸውን ትላንት (ህዳር 20፣ 2005 ዓ.ም) በፓርላማ በመገኘት አሹመዋል:: አዲሱ ካቢኔም ሶስት ም/ጠ/ሚኒስትሮች ሲኖሩት የአራት ሚኒስቴሮችን ሽግሽግም ያካተት ነው:: የቀድሞ ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር ሚኒሰቴር አቶ ጂነዲ ሳዶ ከሃላፊነት በማንሳት በአቶ ሙክታር ከድር ተተክተዋል:: የጤና ጠብቃ እና የንግድ ሚኒስትር ሚኒሰቴር ዲኤታ የነበሩት ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱና አቶ ከበደ ጫኔ  እንደየቅደምተከትል ለሚመሯቸው ተቋሞች ሚኒስቴር ሆነዋል:: የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡

Friday, November 30, 2012

የህወሐት ኢህአዴግ የፖለቲካ ጭንቀት

Uten navn
ኣስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል
ትዝብቴን ብገልፅ (ቁጥር 2)     ከአስገደ ገብረስላሴ ወልደሚካኤል (መቀሌ):- ከጠቅላይ ሚንስተር ህመምና ህልፈተ ህይወት ተያይዞ ሃገራችን በወሬና በስብሰባ እየተናጠች እንደ ከረመች ሁሉም ዜጎች የሚያስታውሱት ነው። ለነበሩ ስብሰባዎችም ብዙ ገንዘብ እንደተጠየቀ የቅርብ ትዝብታችን ነው። ያ አልበቃም ብሎ አሁንም ለአንድ ፓርቲ ህወሐት ኢህአዴግ ለማጠናከር ተብሎ 80 ሚልዮን ህዝባችን፣ ሁሉም የመንግስት ሰራተኛ፣ የህወሃት ኢህአዴግ ፓርቲ አባላትና የአጋር ፓርቲዎች አባላት፣ የከተማ የገጠር ህዝቦች በስብሰባ ተጠምደው እየተናጡ ይገኛሉ።

ለዚሁ ለማስረጃነት ያህል ባለፈው ሳምንታት ከ11/02/05 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ያህል በትግራይ ዘኖች ወረዳዎች ከተሞች ተንቀሳቅሼ ነበር። በተንቀሳቀስኩባቸው ቦታዎች ያየሁትና የታዘብኩት ቢኖር በዚህ ፅሑፌ አንድ በአንድ አርእስት በመስጠት ለአንባብያን እንዲደርስ አድርጌላሁ። የትግራይ ህዝብ 100% በግድ የህወሐት ኢህአዴግ አባል ፓርቲ እንዲሆን እየተገደደ ይገኛል።አሁን ግዜው የመኸር ወቅት ሁኖ የገጠር ህዝብ የዘራውን ሰብል ለማጨድና ለመውቃት ሌት ተቀን የሚረባረብበት ሰዓት ነበር። 

Thursday, November 29, 2012

ሰበር ዜና፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ 3 ም/ጠቅላይ ሚኒስቴሮችን አስተናገደች፣

Ethiopian Plarliament Playing toys
ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) እና የተለያዩ ድህረገጾች ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማርያም ደሳለኝ ሦሥት ም/ጠቅላይ ሚኒስቴሮች እንደሚኖራቸውና ሃገሪቱንም በቡድን እንደሚመሩዋት መገለጹ የሚታወቅ ነው። ከዚያም ተያይዞ ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማርያም ደሳለኝ ሁለት ተጨማሪ ም/ጠቅላይ ሚኒስቴሮችን እና አንድ ወሳኝና ቁልፍ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርነቱን ቦታ ለህወሓት በማስረከብ አጸድቀዋል። 

Wednesday, November 28, 2012

አምባገነኖችን እንዴት እንታገል?


ከበትረ ያዕቆብ
የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሞት ተከትሎ በኢህአዴግ ውስጥ የተፈጠረው ትልቅ የአመራር ክፍተትና አሁንም ድረስ ውስጥ ውስጡን የቀጠለው የስልጣን ሽኩቻ አምባገነኑን ስርአት ክፉኛ አዳክሞታል፡፡ 

በኢህአዴግ ቤት ውስጥ የተፈጠረው መጠላለፍ እና በጥርጣሬ አይን መተያየት ከውጫዊው ጫና ጋር ተዳምሮ ዛሬ የ21 ዓመታት ዕድሜ ያስቆጠረውን አንባገነናዊ ስርዓት ለማስወገድ ከምን ግዜውም በላይ አመቺ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡ ይህንንም ከግምት ውስጥ በማስገባት የተለያዩ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝቡ አገዛዙን ለማስወገድ ለትግል መነሳት እንዳለበት ደግመው ደጋግመው ጥሪ እያስተላልፉ ይገኛሉ፡፡  

ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ በማንኛውም ማተሚያ ቤት እንዳይታተም መመሪያ ተላለፈ


“ጋዜጣው ቆሻሻ ይዘት ያለውና አመፅ ቀስቃሽ ነው” አቶ ሽመልስ ከማል በሚኒስትር መአረግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ም/ሀላፊ  “የአቶ ሽመልሽ ንግግር የወረደ ቢሆንም የማተሚያ ችግሩ ጠ/ሚኒስትሩ እንዳስተባበሉት እንዳልሆነ በግልፅ ያረጋግጣል፡፡

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት“  ጋዜጣችን እንዲቋረጥ አቶ ሽመልስ ሊያዙ እንደሚችሉ ቅንጣት አልጠራጠርም” አቶ ዳንኤል ተፈራ የአንድነት ፓርቲ ም/ህዝብ ግንኙነት ኃላፊና የኤዲቶሪያል ቦርድ አባል “ስራችንን አላቆምንም መረጃዎችን በኦን ላይን ሚዲያ ለማሰራጨት ዝግጅታችንን ጨርሰናል” ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ  

በናዝሬት በአንድ አመት ውስጥ ብቻ 4 ከንቲባዎች ተቀያየሩ

ኢሳት ዜና:-በቅርቡ በተደረገ ግምገማ ላለፉት አራት ወራት በስልጣን ላይ ቆይተው የነበሩት የናዝሬት ወይም የአዳማ ዋና ከንቲባ እና ከእኝሁ ባለስልጣን ጋር ግንኙነት አላቻው የተባሉት የከተማዋ የኦህዴድ የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ ከቦታቸው እንዲነሱ ተደርጓል።

ገምጋሚዎቹ የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት የነበሩ ሲሆን ግምገማውም በመልካም አስተዳዳር፣ በከተሞች እድገት፣ በኪራይ ሰብሳቢነትና በልማት ሰራዊት አደረጃጃት ላይ ያተኮረ ነበር።

ተቃዋሚ ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ላለመውሰድ ወሰኑ

ኢሳት ዜና:-በ2005 ዓ.ም ለሚደረገው የአዲስ አበባ ከተማና የአካባቢ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ላይ ከፓርቲዎች ጋር ለመነጋገር በአዳማ ከተማ ምርጫ ቦርድ በጠራው ስብሰባ ፒቲሽን የተፈራረሙት የ34 ፓርቲዎች ህብረት፤ የምርጫ ችግሮች ሳይፈቱ  የመወዳደሪያ ምልክታቸውን እንደማይወስዱ በአንድ ድምጽ መወሰናቸው ታወቀ፡፡

የዶላር ዋጋ እየወደቀ ነው ተባለ


ኢሳት ዜና:-የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ በ17 በመቶ ጨምሮ በ16.35 ብር እንዲመነዘር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መወሰኑ ይፋ ከተደረገበት መስከረም 2003 ዓ.ም. ወዲህ ባሉት ሁለት ዓመታት፣ የብር ምንዛሪ አቅም እየቀነሰ ከ10 በመቶ በላይ ወርዷል ሲል የዘገበው ሪፖርተር ነው።

በኅዳር 2004 ዓ.ም. የየዕለቱ የውጭ ምንዛሪ ዋጋን በሚያመለክተው መረጃ መሠረት የአንድ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 17 ብር  ከ20 ሳንቲም የነበረ ሲሆን፣ በኅዳር 2005 ዓ.ም. ያለው መረጃ የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ ወደ 18. ብር ከ20 ሳንቲም ከፍ ብሎአል፡፡

ባለፉት 10 አመታት በአዲስ አበባ የተገነባው ከአጼ ሚኒሊክ ጀምሮ ከተገነባው ይበልጣል ሲሉ አቶ ኩማ ደመቅሳ ተናገሩ

ኢሳት ዜና:-ከንቲባው ይህን የተናገሩት  በቅርቡ የአዲስ አበባ 125ኛ አመት ክብረ በአል ሲጠናቀቅ ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ነው። አቶ ኩማ ከተማዋን የቆረቆሩትን እና በከተማዋ ላይ አሻራቸውን ያሳረፉትን በሙሉ በማውገዝ የኢህአዴግን ስራ ለማሞካሸት ሞክረዋል።

በነገሥታቱ ዘመን የከተማዋ የመሬት ይዞታ ለመኳንንት፣ ለመሳፍንትና ለጦር አበጋዞች ተከፋፍሎ አብዛኛው የከተማዋ ነዋሪዎች ሲሰቃዩ እንደኖሩ፣ የከተማዋ ዕድገት ማስተር ፕላንን ያልተከተለ በመሆኑና በመኳንንቱና በመሳፍንቱ ግላዊ ፍላጐት ተወስኖ ቆይቷል ሲሉ ነው ከንቲባው የገለጹት።

Tuesday, November 27, 2012

በአላማጣ ታፍነው የተወሰዱ ከ20 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም

ኢሳት ዜና:-በራያና አዘቦ ፣ በአላማጣ ከተማ ከኤልክትሪክ መስመር መቃጠል ጋር በተያያዘ በጥርጣሬ የተያዙ ከ20 በላይ ግለሰቦች ወደ ማይጨው ከተማ ተወስደው መታሰራቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ቢናገሩም ፣ ዘመዶቻቸው እንዳይጠይቋቸው በመደረጉ ስለደህንነታቸው ሁኔታ ለማወቅ አልተቻለም።

ወጣቶች የታሰሩት ለኢንቨስተሮች ተብሎ የተዘረጋውን የኤልክትሪክ ምሰሶ አቃጥላችሁዋል በሚል ነው። የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጡት ታፍነው የተወሰዱት ወጣቶች በእስር ቤት ጉዳት ሳይደርስባቸው አልቀረም። በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናትን ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

በራስ አሉላ አባነጋ ስም የተሰየመው ት/ቤት በመለስ ዜናዊ ተቀየረ (ከእየሩሳሌም አርአያ)

በትግራይ ተምቤን - አቢይ አዲ የሚገኘውና በጀግናው ራስ አሉላ አባነጋ ስም ተሰይሞ የቆየው የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ስያሜው ተቀይሮ በመለስ ዜናዊ ስም እንዲሰየም መወሰኑን ታማኝ ምንጮች አስታወቁ።

በደርግ ዘመን የተሰራውና በራስ አሉላ ስም ተሰይሞ የ 9 – 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር ከቆየ በኋላ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ የት/ቤቱን አቅም ለማሳደግ በሚል የ11-12ኛ መመሪያ ክፍሎችን ለመገንባት በአገር ውስጥና በውጭ አገራት የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆች ገንዘብ አዋጥተው ስራው መከናወኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል። ግንባታው ተጠናቆ ባለፈው ነሃሴ ወር ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ እንዳለ አቶ መለስ በማለፋቸው ፕሮግራሙ መሰረዙን ሲታወቅ; ከሁለት ሳምንት በፊት በተከናወነው የምረቃ ስነ-ስርአት የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት በስፍራው እንደተገኙ ማወቅ ተችሎዋል።