Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, December 22, 2012

የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል” የምሥረታ መግለጫና ሃገራዊ ጥሪ

 http://www.ginbot7pf.org/wp-content/themes/ducos/js/timthumb.php?src=http://www.ginbot7pf.org/wp-content/uploads/2012/12/GPF-Pict-4.jpg&w=577&h=220


 የወያኔን ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ በትጥቅ ትግል ለማስወገድ “የግንቦት7 ሕዝባዊ ኃይል” የሚል ስያሜ የሰጠነውን፣ በሃገር ወዳድና ለህዝብ ተቆርቋሪ በሆኑ ወጣቶች፣ ምሁራንና ዜጎች የተሞላውን ድርጅት መመሥረታችን በዛሬው እለት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በይፋ እናበስራልን።

የህወሓት የብረት መዳፍ


(ተመስገን ደሳለኝ)
የድህረ-መለስ ዝግመተኛውና መቋጫ ያጣው የፖለቲካ ማዕበል፣ አሁንም አዳዲስ ክስተቶችን ማሳየቱን አላቋረጠም፡፡ ዝነኛው ‹‹የመለስ ራዕይ›› መፈክርም ግንባሩን የታሰበውን ያህል ወደ አንድ ለማሰባሰብ አቅም ያጠረው ይመስላል፡፡ ጥገናዊ ለውጦቹም እንዲሁ አትራፊ መሆን አልቻሉም፡፡ መሀል አራት ኪሎ በሚገኘው የኢህአዴግ ጽ/ቤት ግድግዳ ላይ የተሰቀለው የመለስ ፎቶም ‹‹ሸምጋይ›› አልሆናቸውም፡፡ 

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና አንድነት ጉባኤ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ።

ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፤ በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።”


      (DEC. 21/2012 ታኅሣስ 12/2005 ዓ/ም/ PDF):- በዚህ ታሪካዊ የዕርቀ ሰላም ንግግር ላይ ከኢትዮጵያና ከአሜሪካ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተሰይመው የተላኩት ልዑካን በፍጹም መከባበር ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሰላምና አንድነት በስፋት ተወያይተዋል።

Wednesday, December 19, 2012

ሽጉጥ ያስመዘዘ የሰበካ ጉባኤ ምርጫ

ከዳዊት
Gibi Gebriel Ethiopian Orthodox church
(አንድ አድርገን ታህሳስ 9 2005 ዓ.ም)፡- በመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል  ገዳም (በተለምዶ ግቢ ገብርኤል) እየተባለ የሚጠራው የቤተክርስትያን ቅጥር ውስጥ  በምዕመናን እና በገዳሙ አመራሮች መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ድንጋይ መወርወሩንና የገዳሙ ገንዘብ ቤት ኃላፊ የሆኑት መምሬ ንጉሴ የታጠቁት ሽጉጥ መምዘዛቸውን በስፍራው የነበሩ የአይን እማኞች ተናግረዋል፡፡
ምዕመናኑንና የገዳሙን አመራር ለልዩነት የዳረገው ምክንያት የሰበካ ጉባኤ አባላት አመራረጥ ሂደት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ እንደ መረጃ ምንጮቻችን በ2003 ዓ.ም ወርሃ መጋቢት በተደረገ ምርጫ ዘጠኝ አባላት ያሉት ሰበካ ጉባኤ የገዳሙንና የሃይማኖቱን ቃለ አዋዲ በጠበቀ መልኩ ወደ ስራ ገብተው ነበር፡፡ ከአዲሱ ሰበካ ጉባኤ በፊት የነበሩት የሰበካ ጉባኤ አባላት የገዳሙን ገንዘብ በመመሳጠር ሲዘርፉ በመቆየታቸው የተነሳ የስራ ዘመናቸውን ሳያጠናቅቁ እንዲሰናበቱ ተደርገው ነበር፡፡

Monday, December 17, 2012

Children for Sale- KRO Brandpunt

KRO Brandpunt documentary about Dutch / Ethiopian Adoptions. Falsified birthcertificates, falsified relinquishments, false information to court, misleading of parents. Watch the video on Children for Sale-KRO Brandpunt- Part one.

Sunday, December 16, 2012

በማረቃ ወረዳ አንድ ግለሰብ በፖሊስ ተገደለ

ኢሳት ዜና:- ታህሳስ 4 ቀን 2005 ዓም ማንነቱ ያልታወቀው ግለሰብ የተገደለው በወንጀል ተጠርጥሮ ከተያዘ በሁዋላ ነው። ግለሰቡን ተኩሶ የገደለው ፖሊስ በስም አልታወቀም። ይሁን እንጅ የወረዳው ፖሊስ ግለሰቡ ሊያመልጥ ሲል ተገደለ የሚል ምክንያት መስጠቱን ለማወቅ ተችልኦል።

የተርጫ ዞን የፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮሚሽነር አለማየሁ ጦፉ ግድያ መፈጸሙን ባይሸሽጉም ፣ ዝርዝሩን ከስብሰባ እንደወጡ እንደሚሰጡ ቢገልጹም ስቱዲዮ እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ልናገኛቸው አልቻልንም።

በጅጅጋ በዘራችን ብቻ የንግድ ድርጅቶቻችንን ተቀማን በማለት ነዋሪዎች ገለጹ

Jijiga town at night
ኢሳት ዜና:- በሶማሊ ክልል በጅጅጋ ከተማ ተወልደው ያደጉ  በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች፣ የክልሉ ፕሬዚዳንት በአማራ ክልል በመገኘት የብሄር ብሄረሰቦችን በአል አክብረው በተመለሱ ማግስት የንግድ ድርጅቶቻችሁን አስረክቡ እንደተባሉ ገልጸዋል።

ቀደም ብሎ ታይዋን እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የልብስ እና የተለያዩ ሸቀጣሸቀጥ ሱቆችን ከፍተው ሲሰሩ የነበሩ ነጋዴዎች እንደገለጹት፣ መንግስት ሱቆቻቸውን እንዲያስረክቡ ያደረጋቸው ፣ የሌሎች አካባቢ ተወላጆች የንግድ ድርጅቶችን በብዛት ይዘዋል በሚል ምክንያት ለክልሉ ተወላጆች ለማስረከብ ነው።