Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, January 12, 2013

4 አመት የተፈረደባቸው የሜጋው ባለስልጣን በሳምንቱ ከእስር ተፈቱ

ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በሜጋ ኪነጥበባት ኀ/የተ/ግ/ማ እና በቀድሞ ስራአስኪያጁ አቶ ዕቁባይ በርሄ ላይ በመሰረተው ክስ መሰረት አቶ ዕቁባይ አራት ዓመት ከአምስት ወራት ቅጣት ከተላለፈባቸው በኋላ ቅጣቱ በገደብ ተደርጎላቸው ተለቀዋል። የባለስልጣኑ መለቀቅ የፍትህ ሥርዓቱ አድሎአዊነት በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን አንድ የሕግ ባለሙያ ገለጸዋል፡፡

የባለስልጣኑ ዓቃቤ ሕግ ባቀረበው ክስ መሰረት የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አስረኛ ወንጀል ችሎት ጉዳዩን ሲመለከት ቆይቶ ተጠርጣሪዎቹ በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ ናቸው ያላቸው ሲሆን ድርጅቱም ሆነ ግለሰቡ ጥፋተኛ የተባሉበት አንቀጾች የ15 ዓመት ጽኑ እስራትና የ50 ሺ ብር መቀጫን የሚያስከትሉ ቢሆንም ባልተለመደ መልኩ አቶ ዕቁባይ 12 እርከን ዝቅ ያለ ቅጣት ማለትም አራት ዓመት ከአምስት ወራት ፍ/ቤቱ ከማስተላለፉም በተጨማሪ ቅጣቱም በገደብ እንዲያዝላቸው ትላንትና የሰጠው ውሳኔ የፍትህ ስርዓቱን ጥያቄ ውስጥ የሚጥል አሳዛኝ ውሳኔ ነው ሲሉ ባለሙያው ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮቴልኮም በአንድ ዘር ቁጥጥር ስር እየገባ መሆኑ ታወቀ

ኢሳት ዜና:-የግንቦት ሰባት የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ  ባወጣው ጥናት እንዳመለከተው በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ኢትዮ ቴልኮምን ከነጻ ኩባንያነት አውጥቶ የአንድ ብሄር መሰባሰቢያና የስለላ ተቋም አድርጎታል።

በድርጅቱ ውስጥ ኤን አንድና ኤን ሁለት የሚባሉ ከፍተኛ የአስተዳደር እርከኖች መኖራቸውን ያስታወሰው ጥናቱ ፣ በኤን አንድና ሁለት የተመ ደቡትን በማኔጅመንት ደረጃ ያሉ ኢትዮጵያውያንና ፈረንሳዮችን የሚያጠቃልል ነው።

“የመለስን ሌጋሲ ማስቀጠል የማንችል ከሆነ ህዝቡ እሳት ሆኖ እንዳያቃጥለን እንሰጋለን” ሲሉ የኢህአዴግ አባላት ተናገሩ

ኢሳት ዜና:-በሚስጥር የደረሰን በአዲስ አበባ  የኢህአዴግ ድርጅት ጽህፈት ቤት ያዘጋጀው ሚስጢራዊ ሪፖርት እንደሚያመለክተው  የኢህአዴግ አባላት ከመለስ ሌጋሲ እና ከልማት ጋር የተያያዙ በርካታ ጥያቄዎችን ማንሳታቸው ተመልክቷል።

የኢህአዴግ አባላት  ካነሱዋቸው ሀሳቦች መካከል “  መስመሩን ያላወቁ አባላት ባለበት እንዴት ሌጋሲውን ማስቀጠል ይቻላል? አባሎች ራሳቸው ጀርባቸው መጠናት አለበት፣ ንፋስ ወደ ነፈሰበት የሚነፍሱ ቁጥራቸው እየበዛ ነው፣ የመለስ ሌጋሲ ሊኖር የሚችለው ስርአቱ እስካለ ድረስ ነው፣ የሚስጥር ጠባቂነት ችግር በአመራሩ ከላይ እስከታች አለ፣ አመራሩ ኪራይ ሰብሳቢነትን አምርሮ አይታገልም፣ህወሀት ሀይለማርያምን ማስቀጠል የለበትም ምክንያቱም ታግሎ የመጣ ሰው ነው መምራት ያለበት”   የሚሉት ይገኙበታል።

Thursday, January 10, 2013

የአላማጣ ወረዳ ነዋሪዎች የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰሙ

alamata
ኢሳት ዜና:-በትግራይ ክልል በአለማጣ ወረዳ የሚኖሩ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች  ተቃውሞአቸውን እያሰሙ ያሉት ፣ የወረዳው የቤት አፍራሽ ግብረሀይል አባላት በህገወጥ መንገድ ተስርተዋል ያሉዋቸውን ቤቶች ለማፍረስ በሄዱበት ወቅት ነው።

ተማሪዎች፣ ህጻናት ፣ አዋቂዎች ከጧቱ 3 ሰአት ጀምሮ እስከ አመሻሹ ድረስ መንገዶችን በመዝጋት ተቃውሞአቸውን የገለጡ ሲሆን፣ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ የሚተላለፉ መኪኖች  መተላለፊያዎች ተዘግተውባቸው ውለዋል።