Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Sunday, July 7, 2013

የሰብአዊ መብት ረገጣንና ኢትዮጲያዊውያንን በገዛ ሀገራቸው የዜግነት መብት ያሳጣውን ዘረኛ ሥርዓት በጽኑ እየታገልን አባይም ለመላው ኢትዮጵያውያን በሚጠቅም መልኩ ይገደባል።


አገራችን በዓባይና በመጋቢ ወንዞች ላይ ግድብ ለመሥራት ሙከራ ስታደርግ ይህ የመጀመሪያው አይደለም። 1959 / (..) በግብፅና በሱዳን መሃል በተናጠል የተደረገውን ስምምነት በመቃወም አስር ሚሊዮን ዶላር በመመደብና በአሜሪካ ሙያተኞች አማካኝነት አያሌ ግድቦችን ለመገንባትና የውሃ ሃብቷን ለመስኖ አገልግሎት ለመጠቀም 1964 / (..) ጥናቶችን ማጠናቀቋን መጥቀስ ይቻላል።

የዚህን ዓይነት ብሔራዊ ጉዳይ ለማስፈጸም ወያኔ ብቻውን አመራሩን ጨብጦ በአገር ውስጥም ሆነ ውጪ ያለነውን ዜጎች በማስገደድም ይሁን በማታለል ገንዘባችንን ለመሰብሰብ ሲነሳሳ እኛም እንደ ዜጋ ይህ ወቅት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሙሉ መብቱ ከምን ጊዜውም በላይ ተጠብቆና ተከብሮ በአገሩ ኮርቶ በፈቃደኝነትና በደስታ የሚሳተፍበት እንዲሆን እንፈልጋለን።