Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, October 13, 2012

ሟቹ ጠቅላይ ሚንስትር ለኤርትራ ተቃዋሚዎች ባህር ዳር ላይ የጀምረውት የነበረው የሬዲዮ ጣቢያ ግንባታ ተቋረጠ

Radio station

መለስ ዜናዊ ስልጣን ላይ በቆየባቸዉ አመታት ያከናውናቸው የነበሩት በርካታ ጉዳዮችን ለፓርቲውም ሆነ ለሚንስትሮች ምክር ቤትም ወይም ለይስሙላ ፓርላማ እንደማያሳውቅ ምንጮች አጋለጡ::ምንጭ አክሱማዊት በፌስቡክ እንዳወረሰችን


ኢትዮጵያ አገራችንን ለ21 አመታት የገዛው ዘረኛውና አምባገነኑ መለስ ዜናዊ ከፍተኛ በጀት የሚጠይቁ ትላልቅ ውሳኔዎችን በዙሪያው ላሰባሰባቸው የካቢኔ ምንስትሮችም ሆነ ለፓርላማው ሳያሳውቅ በራሱ ፈቃድ ብቻ ያስተላልፍና ያስፈጽም እንደነበረ ጉዳዩን በቅርበት ይከታተሉ ከነበሩ ሚንስተሮች የተገኘ መረጃ አጋለጠ።

መለስ ዜናዊ በህይወት በነበረበት ወቅት ለማንም ሳያማክር በግል ሥልጣኑ አስጀምሮት ከነበሩ ፕሮጄክቶች አንዱ ለኤርትራ ተቃዋሚዎች ይሰጥ የነበረው የፋይናንስና የማቴሪያል እርዳታ እንደነበረ የገለጹ ምንጮች የርሱን መሞት ተከትሎ ተቃዋሚዎቹ ከፍተኛ ችግር እንደገጠማቸው ገልጸዋል።

በጋምቤላ የሚንቀሳቀሰው የናይሎቲክ ህዝቦች ንቅናቄ፤ ሰሞኑን ከኢትዮጲያ መንግስት ወታደሮች ጋር መጋጨቱ ተገለጸ

ኢሳት ዜና:-የኢሳት ተባባሪ ዘጋቢ ጋዜጠኛ አግዋ ጊሎ፤ የጋምቤላ ምንጮችን በመጥቀስ እንዳመለከተው፤ በቅርቡ በተካሔደው ግጭት አንድ የመከላከያ ሠራዊት አባል ሲገደል፤ ሶስት ደግሞ እንደቆሰሉ ታውቋል።

Sunday, October 7, 2012

ከፖለቲካ ፍጥጫው በስተጀርባ (ከእየሩሳሌም አርአያ)

Journalist Araya
በገዢው ሰፈር ጎራ ለይቶ ከተለኮሰው የቡድን ፖለቲካዊ ፍጥጫ እና ሴራ ጀርባ አገር እና ህዝብን የሚጎዳ አደገኛ ተግባር በግልጽ እና በስውር እየተካሄደ እንዳለ ከተለያዩ የፓርቲው ምንጮች የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ ።

በተለይ በብአዴን እና በህወሃት ቱባ አመራሮች መካከል ስር ሰዶ የቆየው እና የአቶ መለስን ህልፈት ተከትሎ ያገረሸው የውስጥ ሽኩቻ ሁለት ቡድኖች የሃይል አሰላለፋቸውን ለማጠናከር«ይረዱናል » የሚሏቸውን የሌሎች ፓርቲ ሹማምንት እና የመከላከያ የጦር አዛዦች ከጎን የማሰለፉን ተግባር ቀጥለውበታል።ለግንዛቤ እንዲረዳ የሃይል አሰላለፉን በጥቂቱ በመዳሰስ ወደ ዋናው ነጥብ እናምራ ።

ከበረከት እና ዓዜብ ጎን በመሰለፍ ቀዳሚ የሆኑት አቶ ተፈራ ዋልዋ እና አዲሱ ለገሰ ናቸው።አቶ አዲሱ በይፋ ከሚታወቀው የአየር መንገድ የቦርድ ሃላፊነታቸው ባሻገር ኮተቤ መስመር በሚገኘው እና «የአቢዮታዊ ዲሞክራሲ ማኔጅመንት ት/ቤት »ተብሎ በተከፈተው ተቋም ዋና ሃላፊ እና ለባለስልጣናት እንዲሁም ካድሬዎች መምህር ጭምር ናቸው ። ከመለስ መታመም ወዲህ የህወሃት ካድሬ ላልሆኑ በአቶ አዲሱ እየተሰጠ ያለው ፖለቲካዊ ትምህርት ሳይሆን የበረከትን አቋም የሚያቀነቅን እና ህወሃትን የሚያጥላላ ቅስቀሳ ሆኖአል ።