Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, August 4, 2012

በደቡብ ክልል በፕሬዚዳንቱና በአፈ ጉባኤዋ መካከል በተፈጠረው ውዝግብ ምክር ቤቱ ለሁለት ተከፈለ

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ባለፈው ማክሰኞ የክልሉ ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከሲዳማ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ የአገር ሽማግሌዎችን ሰብስበው “የሲዳማ ጥያቄ ፣ ወቅታዊ አለመሆኑንና አብዛኛውን ህዝብ የማይወክል መሆኑን” ተናገሩ በማለት ለማግባባት ሞክረው እንደከሸፈባቸው መዘገባችን ይታወሳል።

ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ከሌሎች የመገናኛ ብዙሀን የተወከሉ ጋዜጠኞች በስፍራው ተገኝተው “የሲዳማ ጥያቄ  የጸረ ሰላም ሀይሎች ጥያቄ ነው” በማለት ይዘግባሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ ስብሰባው በውዝግብ ተደምድሟል።

ይህን ተከትሎ ፕሬዚዳንቱ የዞኑን እና የወረዳዎችን ከፍተኛ ባለስልጣናት ትናንት ሰብስበው፣ ህዝቡን የማሳመን ስራ በበቂ ሁኔታ ባመለስራታችሁ ተጠያቂዎች ናቸው ብለው ሲናገሩ፣ የዞኑ አፈ ጉባኤ የሆኑት ሴት ” የህዝቡ ጥያቄ በህገመንግስት የተቀመጠ ጥያቄ ነው ይህንን በህገመንግስት የተቀመጠ መብት፣ አይገባህም ብለን ልናሳምን አቅሙም የለንም፣ አንችልምም፣ ይህ ጥያቄ እኮ የኔም ጥያቄ ነው።” በማለት መልሰዋል።

የአፈ ጉባኤዋን መልስ ተከትሎ አብዛኛው የምክር ቤት አባላት ” እኛ ጥያቄው የህዝብ ነው፣ ከህዝብ ጋር የምንጣላበት ነገር አይኖርም ፣ ህዝቡን መብታችሁን አታስከብሩ በማለት አንቀሰቅም” በማለት በሀይለቃል መናገር በመጀመራቸው ስብሰባው ያለውጤት እንዲበተን ተደርጓል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰሞኑን በዞኑ በርካታ ተነሱ የሚል ይዘት ያላቸው ወረቀቶች በብዛት እየተሰራጩ ነው። የዞኑ ባለስልጣናት እርስ በርስ መከፋፋላቸውን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተለው ዘጋቢያችን ገልጧል።

No comments:

Post a Comment