Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, April 21, 2012

ጠቅላይ ሚንስትሩና ንቀታቸው!!

 By ተሻገር ምትኩ
ጠቅላይ ሚንስትሩ ለተወካዮች ምክር ቤት የሰጡትን ንግግር በሃፍረት ተሞልቼ ከጎደኞቼ ጋር ሳየው ቆየሁ። በሚገርም ሁኔታ ያሳፍራል። እንዴት ኣንድን ሃገር በሃላፊነት መራለሁ ከሚል ግለሰብ እንደዛ አይነት የወረደ ንግግር ይደመጣል? ያው እኔም እሱ የፈጠረኝ ትውልድ ስለሆንኩ ያሉት ባይገርመኝም እንዴት አንድ ሰው በ 20 አመት ውስጥ እራሱን ጠብቆ መናገር ያቅተዋል? 

እኛ አማሮች ላይ ያሉት ላይ እመለስበታለሁ ግን በትንሹ ስለኣስተማሪዎች የተሰጠውን አስተያየት ስላናደደኝ ትንሽ ልበል። እዚህ ላይ አንድ ነገር ካላልኩ በጣም እወዳቸው የነበሩትን አስተማሪዎቼን የማዋርድ ስለመሰለኝም ጭምርም ነው።

አስተማሪዎች የተከበሩና ትውልድ ለመቅረጽ የሚጫወቱትን ሚና ለኣንባቢ በማስረዳት ማሰልቸት ኣልፈልግም። ግን እንበልና (ጠቅላይ ሚንስትሩ እንዳሉት) ከብዙ ሺ አስተማሪዎች ጥቂቶች መጥፎ ናቸው እንበል። እነዛ ግን በደካማነታቸው ስንት ሰው ጎድተዋል? 10 ሰው? 100 ሰው? 1000 ሰው? ምናልባተም በ አስር ሺዎች እንበል። ጠቅላይ ሚንስትሩና የሳቸው ጠባብ ፖሊሲ ኣንድ ትውልድ ደምስሶ ሁለተኛውን እያደነቆረ እንደሆነ አያውቃሉ? እሳችው ደካማ ሚልዋቸው አስተማሪዎች ስለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሚሉትን ሰምተዋል? እንደሰማሁት ከሆነ ማይክራፎን ብዙ ግዜ ሲይዙ መስማት ይከብዳል ሲሉ እንጅ እስካሁን እውነት አልመሰለኝም ነበር።

ስለኛ አማሮች ደሞ ሲያወሩ ፡ ያው የለመደባቸውን ቤት ያፈራውን ከፋፍለህ ግዛን ሊጠቀሙብን የሞከሩ ይመስላል። ሲናገሩ “ምስራቅ ጎጃም” የሚለወን ቃል መጠቀማቸው ሌሎች አማሮች አፋችሁን ዝጉ ነው? ወይስ ጉዳዩ ጠቃላላ ኢትዮዽያዊያንን አይመለከትም ለማለት ነው? ያንን እንደወም እንደንቀትና ድፍረት ያዩ ፡ አማራው መደራጀት አለበት ብለው እየገፉበት ይገኛሉ። ስላልተደራጀን አንጠቃለን ሲሉን የነበሩትን ወንድሞቻችንን አሁን ጆሮቻንን ከፍተን መስማት ጀምረናል። ጠ/ሚንስትሩ ሚሉት በጣም ይገርማል ፡ የጉራ ፈርዳን አካባቢ አማሮች ምስራቅ ጎጃም አደረጉት የሚሉን ፣ ከ አንድ አካባቢ የመጡ ህዝቦች በመብዛታቸው የተነሳ የአራት ኪሎ ቤተመንግስቱንና አንዳንድ የ አዲስ አበባን ኣካባቢዎች የምኖች ሰፈር እየተባሉ እንደሚጠሩ ያውቃሉ?

የሰሞኑን የ ጠ/ሚንስትሩን ንግግር ወትሮው እንደምናደርገው ከ ደኞቼ ጋር አብረን ስንከታተለው ነበርን። በየጊዜው ስለሀገራችን ፖለቲካና ስለተለያዩ ጉዳዮች ተገናኝተን ምንወያይበት ሻይ ቤት (ኮፊ-ሀውስ) ተቀምጠን ሳለን ጏደኞቼ የተለመደውን ስድብና ዘለፋ ይሄ ሼባ ምናምን እያሉ ጠ/ሚንስትሩን ስብእና የሚነኩ ነገሮች ሲናገሩ ፡ ሁልግዜ ስራ በዝቶባቸው ነው እያልኩ እንደምከራከርላቸው ከትላንት በስትያ ግን ቃል ሳልተነፍስ ነገሩን ሳዳምጥ ቆየሁ። 

እንዴት ስራ አይብዛባቸው? በዚች ጉዳይ ላይ አስቡት እስቲ ፡ እራሳቸው መርማሪ ፖሊስ ፣ ከዛም አባራሪ ፖሊስ ፣ ባለሙያ ፍርድ ሰጪ(ወረቀት እጨርሳለሁ እንጂ ዝርዝሩ አያልቅም) እያለ ይቀጥላል። እናም እነዢህ ጏደኞቼ ሲያብጠለጥሉዋቸው “ይሄ ሼባ ጉራፈርዳን ምስራቅ ጎጃም አደረጉት ሚለን ሰሜን ጎንደርን ከነ ካርታው የምን ይዞታ አደረጉት እየተባለ እንደሚወራ አልሰማም እንዴ?” እያሉና የተለያየ ነገር በማንሳት ከፍ ዝቅ ሲያደርጉዋቸው አመሹ። ወጣትነት ጥሩ ነው። ከ ጠ/ሚንስትሩ ሚፈልቁትን የወረዱ ሃሳቦች ወይንም በትምህርት አለዛም በእድሜ የማስተካከል እድሉ አለን። ይብላኘ ለሳቸው። 

እኛ ውጣቶች እንደውም ካስፈለገን የ አምስት አመት የ ስብእናና ውርደትን የመከላከል ትራንስፎርሜሽን እቅድ አውጥተን 11 ፐርሰንት እድገት አክለንበት ምናሳካው ይመስለኛል።በሰሞኑ የ ህዝብ ንግ ግር ላይ ጠ/ሚንዝትሩ ያለማፈር እንደዛ ሲተረተሩ እንዴት ከኔና ከኔ ትውልድ ጥሩ ነገር ሊጠበቅ ይቻላል? ይሄ ሁሉ ውሸት አይናቸውን በጨው ኣጥበው ሲዋሹ እኔዴት ቢንቁን ነው? ከሱም ብሶ አጎንብሶ አለ የሃገረ ሰው። 

ጠ/ሚንስትሩ ብሄራዊ ሆነው እኛ አማሮች ተነካን ስላልን ጎጠኞች ተብለን የተፈረጅነው በየትኛው ስሌት ንው? እኔምለው ጠ/ሚንስትሩ በብዙ ሚልዮን የሚቆጠረውን የኢትዮዽያ ህዝብን ትተው በጥቂት ሚልዮን እንደውም ወርደው በመንደርና አካባቢ ተደራጅተው ስልጣ ላይ መፈናጠጣቸውን ረሱት እንዴ? አልፈው ተርፈው ኢትዮዽያን እያስተዳደርኩ ነው እያሉን ዞር ብለው የዛው ኣናሳ ስብስብ መሪ ሆነው እስከዛሬ ህዋሀትን እያስተዳደሩ እንዳሉ ዘነጉት እንዴ? ያም ሆነ ይህ አይደለም በ ፓርላማ ፊት ቢወራጩ ነጠላ ዘቅዝቀው እያለቀሱ ቢነግሩንም ምናምናቸው ከመሰላቸው አዝንላቸዋለሁ። እወነቱን እናውቃለን። እናም ያባረረ ቢረሳም የተባረረ አይረሳም!!!

እኔን ለማግኝት ከፈለጉ ፡ teshagermitiku@yahoo.com በሚለው አድራሻ እገኛለሁ።

የቦብ ማሪሊንን የህይወት ታሪክ የሚዘክር ዘጋቢ ፊልም ተሰራ

ኢሳት ዜና:-
በኦስካር ተሸላሚው ኬቪን ማክዶናልድ የተሰራው ፊልም የቦብ ማርሊን ህይወት ከሚገልጹት ፊልሞች ሁሉ የተሻለ ነው ተብሎአል። ፊልሙ ቦብ ማርሊንን ብሄራዊ ጀግና ለማድረግ ለተጀመረው እንቅስቃሴ እገዛ እንደሚያደርግ ታውቋል።

በኪንግስተን ፓርክ በተደረገው የመክፈቻ ዝግጅት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ጃማይካዊያን ተሳትፈዋል። በዝግጀቱ እለት ለመንግስቱ ባለስልጣናት መረማመጃ ተብሎ የተነጠፈው ቀይ ቢጫ እና አረንጓዴ ባንዲራ ፣ በተመልካቹ ተቃውሞ እንዲነሳ ተደርጓል። እነዚህ ሶስቱ ቀለማት ለጃማይካዊያን የተቀደሱ ቀለማት ናቸው።

በለጋ እድሜው የተቀጨው የሬጌ ሙዚቃ ንጉሱ ቦብ ማርሊን ፣ ጌት አፕ ስታንዳፕ፣ ኖ ውመን ኖ ክራይ በመሳሰሉት ውብ ዘፈኖቹ ይታወቃል።

ከተማ በተፈጠረው ረብሻ ከ5 ያላነሱ ሰዎች በፖሊሶች ተገደሉ


ኢሳት ዜና:-
በጋሞጎፋ ዞን በመለኮዛ ወረዳ በለሀ ከተማ ከአራት ቀናት በፊት በተነሳው ረብሻ ልዩ የፌደራል ፖሊስ እና የመከላከያ አባላት ህዝቡ ላይ በከፈቱት ተኩስ ቁጥሩ በትክክል ለማወቅ ያልተቻለ በርካታ ሰዎች ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል። አንዳንድ የአካባቢው ምንጮች የሟቾችን ቁጥር 10 ሲያደርሱት ሌሎች ደግሞ ወደ 5 ዝቅ ያደርጉታል። በተመሳሳይም በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች ቁስለኞች ሆነዋል፣ ድብደባ የደረሰባቸው እና ለእስር የተዳረጉትም ቁጥራቸው እጅግ በርካታ ነው ተብሎአል።

ግጭቱ የተነሳው ከአከላለል፣ ከማዳበሪያና ከወረዳ ጥያቄዎች ጋር ተያይዞ መሆኑን ለማወቅ ተችሎአል። በጎፋ ዞን የሚኖሩት የመሎ ብሄረሰብ አባላት በጎፋ ዞን ውስጥ  መጠቃለላችን ተገቢ አይደለም የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውን ለማወቅ ተችሎአል። እጅግ የሚያሳዝነው ወታደሮቹ ነዋሪዎችን ከገደሉ በሁዋላ ህዝቡ አስከሬን እንዳይወሰድ መከልከላቸው ነው ሲሉ አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአካባቢው ነዋሪ ለኢሳት ገልጠዋል።

ውጥረቱ አሁንም እንዳለ ሲሆን፣ የፌደራል ፖሊስ አባላትና ወታደሮች ከተማዋን መውረራቸው ታውቋል። ጉዳዩን በማስመልከት የደቡብ ክልል ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። ይሁን እንጅ የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ተወካይ ግጭት የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ግጭቱ መከሰቱን ውጥረቱ አሁንም መኖሩን አረጋግጠውልናል። አቶ ዳንኤል እንዳሉት በደቡብ ክልል ከአከላል ጋር በተያያዘ የሚታየው ግጭት የቆና እና እየቀጠለ ሊሄድ የሚችል ነገር ነው ይላሉ.

በአልቃይዳ ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሸኚዎች እንዳይገቡ አገደ

ኢሳት ዜና:-
አየር መንገዱ ሸኚዎች ወደ ውስጥ እንዳይገቡ ያገደው ከአራት ቀናት በፊት ጀምሮ ነው። የፋሲካ በአልን ለማክበር ወደ ኢትዮጵያ የተጓዙ መንገደኞች ወደ አየር ማረፊያው ሲገቡ ከወትሮው የተለየ ጥብቅ ፍተሻም እየተካሄደባቸው ነው። ተጓዦችን ለመሸኘት የመጡት ግን ወደ ውስጥ እንዳይገቡ ተደርጓል። ወደ ውስጥ ሲገቡና ሲወጡ የሚታዩት ልዩ የይለፍ ወረቀት የያዙ የመንግስት ባለስልጣናት ብቻ ናቸው። በርካታ ሸኚዎች በድርጊቱ ማዘናቸውን አካባቢውን ለጎበኘው የኢሳት ሪፖርተር ገልጠዋል።

አንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን አየር መንገዱ እገዳውን ላልተወሰነ ጊዜ የጣለው አልቃይዳ የሽብር ጥቃት ለመፈጸም መዘጋጀቱን መንግስት መረጃ ስለደረሰው ነው ብለዋል። ሰሞኑን አቶ መለስ በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች የአልቃይዳ ሴል ተገኝቷል ብለው መናገራቸው ይታወሳል፤ ከወር በፊት ደግሞ  የአልቃይዳ አባላት ናቸው የተባሉ 3 ኢትዮጵያውያን  ታስረው ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

አንዳንድ ወገኖች የአልቃይዳ መረብ አለ የሚለውን በጥርጣሬ አይን እየተመለከቱት ነው። መንግስት ከሙስሊም ኢትዮጵያውያን የተነሳበትን ከፍተኛ ተቃውሞ ለመጨፍለቅ አልቃይዳን በማስፈራሪያነት ሊጠቀምበት አስቦአል ይላሉ እነዚህ ወገኖች። ምናልባትም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በአንድ የአረጀ አውሮፕላን ላይ መንግስት እራሱ ያቀነባራረው ጥቃት ሊፈጸም ይችላል የሚሉ ፍንጮችም አሉ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሸኚዎችን ለሳምንት ያክል ሲያግድ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው ተብሎአል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ልዩነቱን አቻችሎ በወያኔ ጠባብ አገዛዝ ላይ በጋራ እንዲነሳ ጥሪ አቀረበ


ኢሳት ዜና:-
እራሱን ህጋዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ሲኖዶስ፤ በሚል የሚጠራው ቅዱስ ሲኖዶስ “ ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ልዩነቱን አቻችሎና አስወግዶ  አገር እያጠፋ ባለው የወያነ ጠባብ አገዛዝ ላይ በጋራ እንዲነሳ ጥሪ አቀረበ።

መቀመጫውን በአሜሪካ ኦክላንድ ያደረገው ሲኖዶሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ሲኖዶስ ባወጣው መግለጫ የጥንቱ የግብጽ አገዛዝ በእስራኤል ልጆች ላይ ሲያደርግባቸው የነበረውን አሰቃቂ ግፍ በማስታወስ፤ያኔ በባርነት ታግተው የነበሩት እስራኤላውያን ህይወታቸው  በምን ደረጃ ላይ እንደነበር ሊያመለክተን የሚችል ነገር ካለ፤ አሁን በኢትዮጵያ ያለው የመከራ ህይወት ብቻ ነው ብሏል።

“ኢትዮጵያ በታሪኳ ገጥሟትና አይታው የማታውቀው ህልውናዋን የማጥፋት እንቅስቃሴ በዘረኛ መርሆ በሚገዛት ወያነ፤ እጅግ በሚገርም ፍጥነት እየተካሄደባት ይገኛል” ያለው የሲኖዶሱ መግለጫ፤አጥፊና ጨካኝ መንግስት ቢሆን እንኳ ፤እንዲህ እንደ ወያነ-  እየረገጠ የሚያስተዳድረውን ህዝብ ይህን ያህል የመሬት ኪራይ የሚያስከፍል አገዛዝ በዓለም ላይ ተፈልጎ አይገኝም”ብሏል።

“በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵየን የሚገዛው ቡድን የአምልኮ ቦታዎችን- እግዚአብሔር የሚመለክባቸው ሳይሆን፤ካድሬዎች የሚመለመሉባቸው አድርጓል፤ኢትዮጵያ የምትታወቅባቸውን ገዳማትና ቤተ-መቅደሶች በሙሉ ደፍሯል፤አዋርዷል። ለዓለም ሰላም ለመለመን በጸሎት የሚተጉ የባህታውያንን መጠጊያ ዋሻዎች በቡልዶዘር እየደመሰሰ፤መጠለያ ዛፎቹን በእሳት እያቃጠለ፣የቅዱሳን አባቶችን አጽም ከመቃብር እያወጣ፣በረሀብና በግፍ አገዛዝ የተንገፈገፈው ህዝብ በአምላኩ ፊት እንኳ ተስፋ እንዳይኖረው ተስፋ የሆኑትን ገዳማቱን በለመደው”ልማት”በሚል የቅጥፈት ቅስቀሳው-እያወደመ፦ ተመልሰው ወደማያንሰራሩበት የጥፋት አዘቅት ውስጥ እየከተታቸው ይገኛል” ብሏል- ሲኖዶሱ።

እንደ ሲኖዶሱ መግለጫ  አገዛዙ ገዳማቱን ወደማፈራረስ እርምጃ የተሸጋገረው፤ የገዳማቱ እንዳለ መቀጠል  እየተከተለ ላለው ዘር ላይ የተመሰረተ ጸያፍ ፖለቲካ እንቅፋት ስለሆኑበት ነው።
“ምክንያቱም…” ይላል መግለጫው ሲቀጥል “….ምክንያቱም ገዳማቱ የዘር ክፍፍልን አያውቁም። የቋንቋ ልዩነትን እንደ ዘር ወስደው ሰውን ከሰው አይለዩም።ሰውን ከሰው አያበላልጡም”ይላል።
“ገዳማቱ የአገሪቱ አንድነትና የመንፈሳዊ ብልጽግና ማዕከል ብቻ ሳይሆኑ፤ የትምህርት ማዕከልም ጭምር ነበሩ” ያለው ህጋዊው ሲኖዶስ፤ የገዳማቱ መኖር ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ጥንካሬና ህልውና ለኢትዮጵያም አንድነትና መሰረት እንደሆነ፤ የወያነ ዘረኛ ቡድን ጠንቅቆ ያውቀዋል”ብላል።

በምርጫ 97 ወቅት የአቅም ግንባታ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ተፈራ ዋልዋ ፦”የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያንን ፦”የነፍጠኞች ዋሻ” ብለው መዝለፋቸው አይዘነጋም። “የገዳማቱ ህልውና መጠበቅ ገዥው ቡድን ሊያጠፋት ቆርጦ በተነሳባት ኢትዮጵያ ላይ እየፈፀመ ላለው የማጥፋት ተግባር ትልቅ መሰናክል እንደሚሆንበት ይረዳል’ያለው ሲኖዶሱ፤ “ለዚህም ነው አንዴ በልማት ስም፤ ሌላ ጊዜ በእሳት ስም ገዳማቱን እያጠፋ ያለው”ብሏል። ሲኖዶሱ መግለጫውን ለማውጣት የተገደደውም፤ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የዋልድባ ገዳምን ለማጥፋት እየተፈጸመ ያለውን ሴራ ለማሳወቅ እንደሆነ ጠቁሟል።

“በመናኙ በአባ ሳሙኤል ዘዋልድ በ 13ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የተቆረቆረው የዋልድባ ገዳም  ፤በአሁኑ ጊዜ ስልጣን ላይ፤ ያለ ኢትዮጵያ ህዝብ ይሁኝታ በተፈናጠጠው ቡድን  ከመደፈሩ በስተቀር፤በቀድሞ የኢትዮጵያ መሪዎችና ነገስታት ይቅርና  በጠላትም ያልተደፈረ ታላቅ የአገሪቱ መንፈሳዊ እሴት ሆኖ የኖረ ገዳም ነው” ሲል ሲኖዶሱ አትቷል። ሲኖዶሱ አያይዞም፤የአሁኑ መንግስት  በገዳማት ላይ እየፈጸመ  ካለው ጥፋት በመነሳት ፤”የኢትዮጵያ፦ የመጥፊያዋ -መደምደሚያ ጅማሬ ፤እየተደገሰ ነው” ብሎ እንደሚያምን ስጋቱን ገልጿል።

በስደት ላይ የሚገኘው  ይህ ሲኖዶስ የህወሀትን አጥፊነት ቀደም ብሎ ስላወቀው ጥፋቱን እያጋለጠ ስህተቱን በማያሻማ መንገድ ሲያወጣ ሀያ ዓመታት ማስቆጠሩንም አውስቷል። ሲኖዶሱ በመቀጠልም፦”ቤተ-ክርስቲያንን ከፖለቲካ ጋር ምን ያገናኘዋል?ብለው ለሚጠይቁ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ጩኸት ግልጽ የሆነ ይመስለናል።የወያነ ጠባብ የገዥ  ቡድን አጥፊነት የመጨረሻው ጣራ ላይ ደርሷል።በአሁኑ ጊዜ አጥፊነቱን አልተረዳሁም የሚል ያለ አይመስለንም።

የወያነ ጠባብ ቡድን እስካለ ድረስ፤ኢትዮጵያ የምትባል አገር በስምም፣በአካልም በመልክዓ-ምድር ላይ ትኖራለች ብሎ የሚያስብ ካለ፤ አንድም እሱ የዋህ ነው፤አለያም የጠባቡን ገዥ ቡድን ዓላማ የሚጋራ ነው።”ብሏል። በመሆኑም ኢትዮጵያ እንደ አገር እንድትቀጥል የሚፈልጉ ሁሉ፤ የቤተክርስቲያንን ጥሪ በመቀበል አገራቸውን እንዲታደጉ  በማሣሰብ  የትብብር ትግል ጥያቄውን በስድስት ነጥቦች በመዘርዘር አቅርቧል-ሲኖዶሱ።

በቅዱስ ሲኖዶሱ ዋና ፀሀፊ በብጹዕ አቡነ መልከ-ጼዴቅ ፊርማ ይፋ የሆነው  ይህ መግለጫ፦“በፖለቲካ፣በሀይማኖትና በልዩ ልዩ ችግር የሀሳብ ልዩነት እያደረጋችሁ የምትጣሉ ሁሉ፤ጠባችሁ ስለ አገር ከሆነ፤ አገር የለችም።ስለ ሥልጣን ከሆነም፤ የሚመርጥ ህዝብ -የሚተዳደር አገር ስለሌለ፤ህዝብ ከማለቁ፤ሀገርም ጨርሶ ከመጥፋቱ በፊት በአንድ ልብና በአንድ ሀሳብ መክራችሁ በዚህ የአገር አጥፊ ቡድን ላይ በመነሳት ኢትዮጵያን እንድታድኑ በቤተ-ክርስቲያን ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን” ብሏል።

ትናንት ከጁምአ ጸሎት በሁዋላ ሙስሊሞች አደባባይ በመውጣት ከፍ ያለ ተቃውሞ ማሰማታቸው ተዘገበ

ኢሳት ዜና:-
ትናንት ከጁምአ ጸሎት በሁዋላ በትልቁ አንዋር መስጂድ እና በ አወሊያ ከተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በተጨማሪ፣ በደሴ ከ80 ሺህ እና በሀረር ከ 50 ሺህ በላይ ሙስሊሞች አደባባይ በመውጣት ከፍ ያለ ተቃውሞ ማሰማታቸው ተዘገበ።

ከመቼውም በተለየ መልኩ  የሙስሊሞቹ ተቃውሞ በ አገር አቀፍ ደረጃ  እያየለ የመጣው፤አቶ መለስ ሰሞኑን ፓርላማ ቀርበው  ከሙስሊሙ ማህበረሰብ ለተሰነዘረው ጥያቄ የሰጡት ምላሽ በ እውቀት ያልታገዘ ከመሆኑም በላይ፤ ሆነ ተብሎ ሙስሊሙን ማህበረሰብ እርስ በርሱና ከክርስቲያን ወንድሞቹ ጋር ለማጋጨት የተጠነሰሰ ሤራ በመሆኑ ይበልጥ ስላስቆጣን ነው ብለዋል-አንድ የአዲስ አበባው ሰልፍ አስተባባሪ ለ ኢሳት ዘጋቢ በሰጡት አስተያዬት።

በሁሉም ከተሞች በተካሄዱት ሰልፎች ላይ ጎልተው ሲንጸባረቁ የነበሩት መፈክሮችም፦ ”አንከፋፈልም!  ድምፃችን ይሰማ! መብታችንን ሳናስከብር ወደ ሁዋላ አንመለስም!” የሚሉ ነበሩ።
የአዲስ አበባው ሰልፍ አስተባባሪዎች  ለሰልፈኛው የበተኑት ወረቀት እንደሚያመለክተው፤ በሚቀጥሉት ሦስት ሳምንታት በመላው አገሪቱ በሚገኙ መስጊዶች  በሙሉ ተከታታይና የማያቋርጡ ሰልፎች ይደረጋሉ።

የትናንቱ የአዲስ አበባ ሰልፍ ከተጠናቀቀ በሁዋላ  በሚቀጥሉት ሳምንታት ስለሚደረጉት ሰልፎች ዝርዝር መርሀ-ግብር የያዘውን ወረቀት ለህዝበ-ሙስሊሙ ሲበትን የነበረ አንድ አስተባባሪ በስፍራው ተገኝተው ሰልፉን በዓይነ ቁራኛ  ሲከታተሉ በነበሩ የፌዴራል ፖሊሶች  ይያዛል።

ይሁንና የፌዴራል ፖሊስ አባላቱ  ወረቀት ሲበትን የነበረውን ወጣት በመኪና በመጫን ወደ እስር ቤት ሊወስዱት ሲሞክሩ ሰልፈኛው ህዝብ  በአንድ ላይ ተባብሮ  ፖሊሶቹን በመክበብ በቁጣ፦ “ልቀቁት!ልቀቁት!” እያለ በመጮኹ፤ በሁኔታው ፍርሀት ያደረባቸው ፖሊሶች ወዲያውኑ ወጣቱን ለቀውታል። በምርጫ 97 ወቅት አቶ መለስ ፦”ለአንድ ወር ታግዷል” ያሉትና  ለዓመታት ጸንቶ የቆየው የሰልፍ ክልከላ አዋጅ፤በተያዘው ዓመት በኢትዮጵያ ሙስሊሞች  ተሽሯል።

አቶ መለስ በቅርቡ በሙስሊሞች ጥያቄ  ዙሪያ በፓርላማ ምላሽ ሢሰጡ ‘አክራሪ’ ያሏቸውን ሀይሎች  በነቀፉበት ክፍል ላይ፦”እነዚህ ሀይሎች በግብጽ፣ በቱኒዚያ እና በየመን ያደረጉትን አይተናል” በማለት  በተጠቀሱት አገሮች የተካሄዱትን የአብዮት ለውጦች ከአክራሪዎች እንቅስቃሴ ጋር በማገናኘት በመጥፎነት መፈረጃቸው ብዙዎችን ያስገረመ ሆኗል።

ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ አንድ የመድረክ ከፍተኛ አመራር፦” የአቶ መለስ መንግስት የሙስሊሞችን ጥያቄ መመለስ ያልፈለገው ለምን እንደሆነ አሁን ግልጽ ነው። በቱኒዚያና በግብጽ የተካሄዱትንና ሀያላኑን ጨምሮ መላው ዓለም ያደነቃቸውን ህዝባዊ አብዮቶች አቶ መለስ የአክራሪዎች ውጤት ሊያደርጓቸው ሲሞክሩ ማየት አስቂኝ ከመሆኑም በላይ፤ በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰልፍ ምን ያህል ጭንቀት ውስጥ እንደገቡ ሚያሳይ ነው”ብለዋል።

“ይህን  ተሞክሮና ምክር ያገኙት ከየመኑ አብደላ ሳላህ እንዳይሆን ብዬ እጠረጥራለሁ?” በማለት  እኚሁ  የመድረክ አመራር ተሳልቀዋል። ትናንት በአወልያ የተደረገውን የተቃውሞ እንቅስቃሴ የአልጀዚራ አረብኛ ክፍል ማቅረቡ ታውቋል።

“Land Grabbing” in Ethiopia: Soldiers Poisoning Water Sources, Forcing Thousands off Ancestral Lands and Killing Wildlife

By Cultural Survival Press Release, (CAMBRIDGE, MA) 
On-the-ground reports from Ethiopia reveal the government is stepping up its violence against Indigenous Anuak people. In the past week, sources say the military has attacked civilians in the Gambella region and poisoned water sources, forcing thousands of Indigenous people to leave their homelands. Wild animals are dying as they drink the poisoned water.
 The Ethiopian government is forcibly removing some 200,000 Anuak people from their ancestral lands and then leasing their forests and farms to foreign agro-industrial companies. Human rights organizations, including Cultural Survival, charge that Ethiopia’s “land grabbing” from its own people increases poverty and hunger, even as the country continues to receive more U.S. and foreign relief aid than any other African nation. 

Cultural Survival, a nonprofit organization that defends the rights of Indigenous people, is asking citizens of donor nations—the United States, the United Kingdom and countries of the European Union—to take action today to urge their governments to persuade Ethiopia to halt this forced relocation program. Concerned U.S. citizens can send letters to the U.S. State Department via Cultural Survival’s website, www.culturalsurvival.org/take-action.

The Ethiopian government’s programs of land grabbing and forced relocation of Indigenous people in the Gambella region violate Ethiopia’s constitution and international human rights laws, according to Cultural Survival Executive Director, Suzanne Benally. Driven from their forests, fertile river valleys, and farmlands with no compensation, Anuak families are forced into government-built villages where they have no means of survival; the promised jobs, farmland, healthcare and schools have not appeared. The relocated Anuak families must depend on the government for food aid, most of which comes from Western governments. Foreign companies’ bulldozers are not only destroying Indigenous people’s farms, they are also destroying Gambella’s last remaining forests and wetlands, even inside Gambella National Park. 

Now, new reports indicate that the government has deployed more than 20,000 troops to Gambella. Cultural Survival has received reports of extra-judicial killings of unarmed Anuak youth. Hundreds of young people are fleeing to neighboring South Sudan and Kenya, fearing that another genocide like the one that occurred in 2003 may be coming. Obang Metho, an Anuak refugee who directs the Solidarity Movement for a New Ethiopia, based in Canada, says the Anuak people are subjected to increased military harassment, reminding them of a similar escalation of violence that culminated in the 2003 massacre of more than 400 Anuak men. 

“We are very alarmed by these reports of increasing state repression in the context of land-grabbing and forced relocation of Indigenous people,” says Paula Palmer, director of Cultural Survival’s Ethiopia campaign. “It is shameful that U.S. tax dollars could be directly or indirectly supporting such devastating human rights violations,” she says. 

Cultural Survival is monitoring the situation in Ethiopia. For updates or to send letters to governments of the U.S., the U.K., and the E.U, visit www.culturalsurvival.org/take-action. Cultural Survival is a nonprofit organization that has partnered with Indigenous Peoples for 40 years to defend their lands, languages and cultures.  

Contact:
Paula Palmer, Director, Global Response Program, culturalsurvival.org paula@culturalsurvival.org; 303.444.0306 and 303.335.8629 (cell)

የካድሬው የፍቅር ደብዳቤ 3

 By Abe Tockichaw
ይህ ፅሑፍ “አርብ አርብ ይሸበራል ኢየሩሳሌም” በተባለበት በዕለተ ጁምአ ለምትታተመው ፍትህ ጋዜጣ የተሰናዳ  ነው። ከጋዜጣዋ ርቃችሁ ለምትገኙ ወዳጆች ደግም እነሆ በዚህ መልኩ…የፍቅር ደብዳቤውን ያሰናዳው ታታሪ ካድሬ ከዚህ በፊት ቁጥር አንዱን በአውራምባ መፅሔት፣ እንዲሁም ቁጥር ሁለቱን ደግሞ በአውራምባ ጋዜጣ ላይ ታትመውለታል። ዛሬውም የነዛ ተከታይ መሆኑ ነው። እሱም ይበርታ ይበርታ እና ይፃፍ ፤ እርስዎም ይበርቱና ያንብቡለት! 
 
ይድረስ እንደ ሰማህታት ሀውልት በልቤ ውስጥ ለተተከልሽ፣ እንደ መደበኛ ግምገማ ሁሌ ለምታስጨንቂኝ፣ እንደ ድርጅታችን አርማ ዘወትር ለምትታይኝ፣ እንደ ውሎ አበል ለምትናፍቂኝ ውድ ፍቅሬ፤ ለጤናሽ እንደምን አለሽ? መቼም የተዘረጋው የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም እያለ እንከን ያጋጥምሻል ብዬ አላስብም!

የኔ እመቤት እኔ ከድርጅታዊ ስራዬ ጎን ለጎን፤ ዘወትር አንቺን ማሰብ እና ስለ አንቺ መጨነቅ ኦቨር ታይም የማልጠይቅበት በራስ ተነሳሽነት የማከናውነው የየዕለት ተግባሬ ሆኗል። የኔ ውድ ይሄን  ሰሞን  ደግሞ ለምን እንደሁ እንጃልኝ ከእጄ የምታመልጪኝ እየመሰለኝ ስጨነቅ እና ስጠበብ ከርሜልሻለሁ።

ያስያዝሽኝ ፍቅር ህዝባዊ መሰረት እንዳለው ፓርቲያችን የጠነከረ ነው። ቢሆንም ከአንቺ ዘንድ ያለውን ቁርጠኝነት እስከ አሁን ባለማወቄ የተነሳ እሰጋለሁ። ከአሁን አሁን የኪራይ ሰብሳቢነት ባህርይ የተጠናወታቸው ግለሰቦች ወስደው ለግላቸው ያደርጓት ይሆን? ብዬ እጨነቃለሁ።

ያው አንቺም እንደምታውቂው በአሁኑ ግዜ የሁላችንም ዋነኛ ችግር ሙሰኝነት፣ ግለኝነት እና ኪራይ ሰብሳቢነት ነው። ለሰዎች ያለማሰብ ለህብረተሰቡ ያለመጨነቅ የዘቀጠ አሰራር በየቦታው ተንሰራፍቷል። ታድያ ምድረ ኪራይ ሰብሳቢ እንደ መሬት ወረራ ሊቀራመትሽ የሞት ሽረት ትግል ሲያደርግ እየታየኝ ከአሁን አሁን አጣት ይሆን ብዬ እጨነቃለሁ።

የኔ እመቤት ነጋ ጠባ በስስት ነው የምመለከትሽ። በሀገሪቱ ላይ የሚነሳ ማነኛውም ጉምጉምታ አንቺን የሚያሳጣኝ እየመሰለኝ ስጨነቅ ብትመለከቺኝ ታዝኚልኝ ነበር። ጋዜጠኞች የሚያስቡት፣ ፖለቲከኞች የሚናገሩት፣ መምህራን የሚጠይቁት ሁላ እኔ እና አንቺን ለማለያየት ታስቦ ነው ስል እጨነቃለሁ።

የኔ ቆንጆ የአወሊያው ሰላት፣ የዋልድባው ሱባኤ ሳይቀር እኔን ከአንቺ ለመነጠል ሆን ተብሎ የሚጠነሰስ ሴራ እየመሰለኝ ስጋቴ እንደ ዋጋ ግሽበቱ ከእለት እለት እየጨመረብኝ ነው።እውነቱን ለመናገር አንዳንድ ግዜ ሰዉን በሙሉ በአሸባሪነት ክስ ዘብጥያ አውርጄ ብቻችንን የምንኖርባት ምድር ለመፍጠር እመኛለሁ።

አበዛኸው አትበይኝና ማንም እንዲጠጋሽ አልፈልግም። እንኳንስ ሌላ ቀርቶ ጥቃቅን እና አነስተኛ ማህበራት፣ የወጣቶች እና ሴቶች ሊግ፣ እንኳን አንቺን በነፃነት እንዲያቅፉብኝ አልሻም። እኔው ማህበር ልሁንሽ የኔ ቆንጆ፣ እኔው ላደራጅሽ የኔ እመቤት፤ እኔው ልቀፍሽ የኔ ሸጋ። እመኚኝ እሺ ካልሽኝ፤ በአጭር ግዜ መካከለኛ ፍቅር ካላቸው ግለሰቦች ተርታ እንሰለፋለን።

እሳሳልሻለሁ።
ለዚህም ነው፤ ተሳክቶልኝ ከአንቺ ጋር ግንባር ፈጥረን አብረን መኖር እስክንጀምር ድረስ ማንም እንዳያይብኝ፣ ማንም እንዳይረብሽብኝ፤ ብድር እና ቁጠባ ተቋም ውስጥ ላስቀምጣት ይሆን…? ብዬ የማስበው።

እውነቴ ነው የኔ ቆንጆ እንደምታውቂው፤ ከለበስኳት ሱፍ እና ከጥቂት መፅሀፎቼ ውጪ የሚቆጠብ ገንዘብ የለኝም። ሀብቴ አንቺ ነሽ። አንቺኑ ልንከባከብ፤ አንቺኑ ለዘላለም እንድትቆይ ክፉም እንዳይነካሽ፤ በቁጠባ ባንክ ላስቀምጥሽ።

 እናም ከጫጫታውም ከግርግሩም የፀዳሽ ሁኚልኝ። አረ የኔስ ስስት ለጉድ ነው፤ ሰሞኑን ያ ቴውድሮስ ካሳሁን ያወጣው አዲስ ዘፈን ተለቆ፤ ከተማዋን የግሉ ጭፈራ ቤት አስመስሎት የለ? እናልሽ ፍቅሬን በሙዚቃ ሊበጠብጡብኝ ነው እንዴ? ብዬ ለመላው የከተማ ነዋሪ ሙዚቃውን እንዲቀንሱ መመሪያ መስጠት ሲያሰኘኝ ሰንብቶልሻል። እውነቴን ነው የኔ ቆንጆ አንቺ ካልሽኝ አደርገዋለሁ። አንቺን  ለመጠበቅ እንኳንስ ሙዚቃ ወንዛ ወንዙን ሁሉ እገድባለሁ።

አረ ሳልነግርሽ በቅርቡ ጓደኞቼ የዳቦ ስም አውጣላት ብለው አበሳዬን ሲያሳዩኝ ነበር። እንደ አቅጣጫ፤  ሳንጋባ የዳቦ ስም ሊኖር እንደማይችል ግንዛቤው አለኝ። ነገር ግን እውነትም ከወዲሁ ቅደመ ዝግጅት ባደርግ አይከፋም ብዬ አንዳንድ ስሞችን መርጨልሻለሁ።

ሚሊኒየም አበባ

ልክ አንቺን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር እንዳዋልኩ ያኔ ለእኔ አዲስ ጊዜ፤ አዲስ ዘመን እንደመጣልኝ እቆጥረዋለሁ። ያ ግዜ ግን መቼ ይሆን…? በአስተማማኝ ሁኔታ እጄ ላይ ሆነሽ ለሚቀጥሉት አርባ እና ሃምሳ… አረ ያንሳል መቶ አመታት አብረን እንድንኖር እፈልጋለሁ።

ቦንድ አለሜ

ይህንን ስም የመረጥኩልሽ ልማት ላይ ያለሽን ቁርጠኝነት አሳምሬ ስለማውቅ ነው። “እኔ ለአባይ በገንዘቤም በጉለበቴም ዘራፍ እላለሁ!” ያልሽ የልማት አርበኛ መሆንሽን መቼ አጣሁት? ከዛም በላይ ግን አንቺ ማለት ዛሬ በቁጠባ ባንኬ ያስቀመጥኩሽ እና ነገ የምመነዝርሽ ሀብቴ መሆንሽን ለማመላከት “ቦንድ አለም” ብዬሻለሁ።

ህዳሴ ወርቅ

አንቺ ለእኔ አዲስ ህይወት ነሽ። ባለፉት ጨቋኝ ሴቶች ከፍቅር ልማት ርቆ የቆየው ልቤ በአንቺ  እንደሚያገግም አዲስ ራዕይ ይታየኛል። እንግዲህ መቶ ፐርሰንት የእኔ ከሆንሽ ከዚህ በላይ ህዳሴ ከየት ይመጣል?

የኔ እመቤት ይሄ ብቻ አይምሰልሽ በርካታ ስሞችን አዘጋጅቼልሻለሁ። “ግድብ ነሽ፤ ሽብር ይራቅ፣ ልማቴ፣ ሊዝ አዋጄ…” ምን ያላልኩሽ አለ! የአንቺን ይሁንታ ብቻ ላግኝ እንጂ ያዘጋጀኋቸውን ስሞች በሙሉ ከነ ምክንያቶቼ ዘርዝሬ እነግርሽ እና አሳታፊ በሆነ መልኩ ተወያይተንበት አንዱን እናፀድቃለን። በአካሄዴ እንደምትደሰቺ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ።

እመቤቴ፤

በየ አቅጣጫው የተነሱ ፀረ ፍቅር ሃይሎች በተቀነባባረ መልኩ ሊያለያዩን እንደሚያሴሩ አውቃለሁ። አንቺም ይህንን ግንዛቤ ልትወስጂ ይገባል። ማንም ወደዳጅ መሳይ መጥቶ ጥገኛ እንዳይሆንብሽ ጥንቃቄ አድርጊ። ዘንድሮ ማንም የማይታመንበት ሁኔታ ነው ያለው።

ውዴ

እንደምንም ብዬ አውራ ፓርቲሽ ሆኜ ለዘለቄታው አብሬሽ መኖር እስክንጀምር ድረስ ራስሽን ከኒዮ ሊበራል ሀይሎች ጠብቀሽ እና በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ሀይማኖትሽ ፀንተሽ እንደምትጠብቂኝ ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት በመቶ እርግጠኛ ነኝ!

ከሰላምታ ጋር!

ሰሜን ሱዳን ደቡብ ሱዳንን የምትወጋ ከሆነ ዩጋንዳ ጣልቃ እንደምትገባ አስጠነቀቀች

ኢሳት ዜና:-
የዩጋንዳ ጦር አዛዥ የሆኑት አሮንዳ ኒያክሪማ እንዳሉት ሰሜን ሱዳን ደቡብ ሱዳንን ለመውረር ከከጀለች አገራቸው ዝም ብላ አትመለከትም። የጦር አዛዡ የአልበሽር መንግስት የሎርድ ሬዚስታንስ አርሚ  ሰራዊትን ይደግፋል የሚል ክስም አቅረበዋል። የኡጋንዳን መንግስት እየተፋለመ የሚገኘው የሎርድ ሬዚስታንስ አርሚ ፣ ቀደም ብሎ ከመሸገበት የማእከላዊ አፍሪካ ወጥቶ በሰሜን ሱዳን ድንበር አካባቢ ሰፍሮ እንደሚገኝ ባለስልጣኑ ተናግረዋል።

የመለስ መንግስት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያደርገውን በረራ እንዲሰርዝ በማድረግ ለሰሜን ሱዳን መንግስት ግልጽ ወገናዊነት እንዳሳየ እየተነገረ ነው። የአልበሽር መንግስት ልዩ ልኡክ ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር መገናኘታቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል። ሁለቱ አገሮች ወደ ሙሉ ጦርነት የሚገቡ ከሆነና ዩጋንዳ ደቡብ ሱዳንን በመደገፍ ጣልቃ የምትገባ ከሆነ በአካባቢው ያለውን ፖለቲካ ያወሳስበዋል ተብሎ ተሰግቷል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ  ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያድርገውን በረራ ከዛሬ ጀምሮ ማቋረጡን ለማረጋገጥ ተችሎአል። የመለስ መንግስት በወሰደው ውሳኔ በደቡብ ሱዳን ውስጥ ኢንቨስት እያደረጉ የሚገኙትን የሀወሀት አባላትና ደጋፊዎች ሳይቀር ያሳዘነ ጉዳይ ሆኗል። በደቡብ ሱዳን ስራ ለመስራት የገቡ በሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንም በውሳኔው ተበሳጭተዋል። የአቶ መለስ መንግስት የደቡብ ሱዳን መንግስት በጋምቤላ በሚታየው ግጭት እጁ አለበት ብሎ ያምናል። በቅርቡ በጋምቤላ በተካሄደው የሁለቱ አገሮች ውይይት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለደቡብ ሱዳን መንግስት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን መዘገባችን ይታወሳል።

በሌላ ዜና ደግሞ በቅርቡ በጋምቤላ 19 ሰዎች መገዳለቸውን ተከትሎ ሁለት የአኝዋክ ተወላጅ ተጠርጣሪዎች ሰሞኑን በቁጥጥር ስር ውለዋል። አንደኛው ተጠርጣሪ የተያዘው ክልሉን በበላይነት በሚያስተዳድሩት የመከላከያ ሰራዊት በሽጉጥ ከተመታ በሁዋላ ነው። የጋምቤላው ወኪላችን እንዳለው በክልሉ አሁንም ውጥረት እንዳለ ነው፤ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ስራ የመጀመር አዝማሚያ ቢታይባቸውም በተሟላ መልኩ ስራ አልጀመሩም።

 የመከላከያ ሰራዊት አባላት የሚጠረጥሩዋቸውን ነዋሪዎች ሁሉ እየያዙ በማሰር ላይ መሆናቸው በክልሉ ያለው ውጥረት እንዳይበድር ማድረጉን ዘጋቢያችን የላከው ሪፖርት ያመለክታል።
ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ የደቡብ ሱዳን መንግስት ጦሩን ከአወዛጋቢው ሄግሊግ ከተማ ማውጣቱን አስታውቋል። የደቡብ ሱዳን መንግስት  በላከው ፕሬስ ሪሊዝ ለማወቅ እንደተቻለው የአገሪቱ ጦር ከዛሬ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ ይወጣል። ደቡብ ሱዳን መንግስት ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በሚመሩት የሽምግልና ጥረት ላይም ጥያቄ እንዳለውና እንደገና መመርመር እንዳለበት ጠይቋል።

Friday, April 20, 2012

የፍትህና የነጋድራስ ጋዜጣ አዘጋጆች ፍርድ ቤት ቀረቡ

ኢሳት ዜና:-
የፍትህና የነጋድራስ ጋዜጣ አዘጋጆች ፍርድ ቤት ቀረቡ፣ በፍትህ ጋዜጣ ላይ ተጨማሪ አቤቱታ ቀርቧል::  በእነአንዷለም አራጌ የክስ መዝገብ የፍርድ ቤት ዘገባን አዛብተው አቅርበዋል በማለት የፌዴራል ዐቃቤ ህግ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት አቤቱታ ባቀረበባቸው መሠረት መልስ እንዲሰጡ ፍርድ ቤት የተጠሩት የፍትህና የነጋድራስ ጋዜጦች ዋና አዘጋጆች በጽሑፍ ምላሽ ሰጡ፡፡

በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ችሎቱ ቢሰየምም፣ የፍትህ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ያቀረበው የፍርድ ቤት የመልስ ወረቀት እያንዳንዱ ገጽ በአንድ ገጽ ያልታተመ በመሆኑና በጀርባ ገጽ ጭምር መታተሙ አግባብ አይደለም ያለው ፍርድ ቤቱ፣ የነጋድራስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ሱራፌል ግራማ በበኩሉ በቃል መልስ ለመስጠት በመምጣቱ በአግባቡ በጽሑፍ እንዲያቀርቡ ትዕዛዝ የሰጠው ፍርድ ቤቱ ለከሰዓት 8፡30 ተቀጥሮ ችሎቱ ተበትኗል፡፡

በከሰዓት በኋላው ችሎት ፍርድ ቤቱ የሁለቱን ጋዜጣ ዋና አዘጋጆች የመልስ ወረቀት የተቀበለ ሲሆን ግራ ቀኙን አይቼ ውሳኔ ለመስጠት ለሚያዚያ 16 ቀን 2004 ዓ.ም ጠዋት 2፡30 ተለዋጭ ጊዜ ቀጠሮ ሰጥቻለሁ ብሎ ውሳኔ ያስተላለፈ ሲሆን ዐቃቤ ህግ በፍትህ ጋዜጣ ላይ በተለይ አብሮ የሚሄድ ሌላ አቤቱታ አለኝ በማለቱ ፍርድ ቤቱ ተቀብሎታል፡፡ የፌዴራል አቃቤ ህግ- በተመሳሳይ የምናቀርበው አቤቱታ ተያያዥ ስለሆነ ከቀጠሮው በፊት ከቀድሞው አቤቱታ ጋር እንዲያያዝልንና የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅም አሁኑኑ በቃል መልስ እንዲሰጡልን እንዲደረግ እንጠይቃለን በማለት ዝርዝሩን በንባብ አሰምቷል፡፡ ዐቃቤ ሕግ- በቀድሞው አቤቱታችን እንደገለጽነው በተለይም ፍትህ ጋዜጣ የፍርድ ቤት ተግባርን ጥርጣሬ ውስጥ በሚከት፣ የዐቃቤ ህግ የክስ አቀራረብን የፈጠራ ሥራና የሀሰት አስመስሎ በዘገባ በማቅረብ በፍርድ ሂደት ላይ ባለ ነገር ላይ የቅድሚያ ብይን ሰጥቶ የፍርድ ሥርአቱን ክብር አጉድፏል ብሏል፡፡

አሁንም ይህ የጋዜጣው ተግባር ያልቆመ ሲሆን ባለፈው ሳምንት በሚያዚያ 5 ቀን 2004 ዓ.ም እትሙ ገጽ 4 ላይ “ማቆሚያ ገደብ ያጣው የምስኪኗ እናቴ እንባ” በሚል በክንፈሚካኤል ደበበ ከቃሊቲ ወህኒ ቤት ተብሎ በቀረበው ጽሑፍ ከመጨረሻው 2 አንቀጾች ከፍ ብሎ በሚገኘው አንቀጽ- “ምስኪኗ እናቴ ሚሊዮኖችን በግፍ ውሳኔያቸውና ፍርዳቸው አስነብተውና አስለቅሰው እንዳለፉት የንጉሱና የደርግ ዘመንኞች ሁሉ የዛሬውም የነርሱ ተተኪ የሆኑት የአምባገነኑ ኢህአዴግ ፍርድ ቤት ዳኞች በእኔ በልጇ ላይ የሚበይኑትንና የሚያነቡትን ግፍና ጭካኔ የተሞላበትን የፍርድ ውሳኔያቸውን ለመስማት ወደዚህ ፍርድ ቤት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል በመመላለስ ላይ ናት፤ እነሱም ይህን የግፍ ፍርዳቸውን በማንበብ እንደሚተባበሯት ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ 

 እንደሷ ሁሉ እኔም ለመስማት ጓጉቻለሁ ” ብሎ መጻፉን በንባብ አሰምቶ ይህ የፍርድ ቤቱንና የዐቃቤ ህግን ክብር የሚነካ ነው ብሏል፡፡ በዚህ ላይ አስተያየትህ ምንድን ነው ብሎ ፍርድ ቤቱ የጠየቀው የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ- እኔ መልስ ልሰጥ የመጣሁት ዐቃቤ ህግ ቀደም ሲል ባቀረበብኝ አቤቱታ ላይ ተመስርቼ ነው፡፡ ይህን አዲስ የተናጠል አቤቱታ ገና አሁን ማድመጤ ነው፣ ስለዚህ አሁን ምንም ዓይነት መልስ ለዚህ መስጠት እቸገራለሁ፤ ስለዚህ ከድርጅቱ ጠበቃ ጋር ተነጋግሬ በቀጠሮው መልስ እሰጣለሁ፣ አሁን አልተዘጋጀሁበትም በማለት መልስ ሰጥቷል፡፡
ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኝ ተነጋግሮ ቀደም ሲል የያዘውን የውሳኔ ቀጠሮ ፣ ሚያዚያ 16 ቀን 2004 ዓ.ም ፣ አለመሰረዙን ገልፆ ተጨማሪ ትዕዛዝ በንባብ አሰምቷል፡፡ የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ ዐቃቤ ህግ በተጨማሪ ላቀረበበት አቤቱታ ከቀጠሮው በፊት በሬጂስተራር ጽ/ቤት በኩል በጽሑፍ መልስ እንዲሰጥና ፍርድ ቤቱም አንድ ላይ ግራ ቀኙን ተመልክቶ በእለቱ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ አስታውቆ ችሎቱ ተበትኗል፡፡ በእለቱ የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅን የፍርድ ቤት ውሎ ለመከታተል በርካታ ወጣቶችና የህግ ባለሙያዎች በሰፊው ፍትህ አዳራሽ የታደሙ ሲሆን ጋዜጠኛውንም አበረታተውታል፡፡

የፍትህ ጋዜጣ ለፍርድ ቤት ያቀረበው መልስ እጃችን ላይ የገባ ሲሆን በአጠቃላይ ይዘቱ ተመስገን በአቃቢ ህግ የቀረበበትን ክስ ውድቅ አድርጓል። ተመስገን ደሳለኝ ለፍርድ ቤት ያቀረበውን መልስ በድረ ገጻችን ላይ ማንበብ እንደሚችሉ ለማስታወቅ እንወዳለን። ኢሳት ብርሀንና ሰላም ማተሚያ ቤት ጋዜጦችን ሳንሱር ለማድረግ አዲስ መመሪያ ማውጣቱን መዘገቡ ይታወሳል። ኢሳት ብርሀንና ሰላም ማተሚያ ቤት ጋዜጦችን ሳንሱር ለማድረግ አዲስ መመሪያ ማውጣቱን መዘገቡ ይታወሳል።

  

                                                                                            

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያደርገውን በረራ አቋራጠ

ኢሳት ዜና:-

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያደርገውን በረራ አቋራጠ የደቡብ ሱዳን መንግስት ተቃውሞውን ቀጥሎአል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለደቡብ ሱዳን ባለስልጣናት ኦፊሴላዊ የጉዞ ማመላለሻ መሆኑ በተነገረ በወራት ውስጥ፣ ወደ አገሪቱ ዋና ከተማ ጁባ እና ወደ ማላካ የሚደረገው በረራ እንዲቋረጥ ተደርጓል። ጁባ ከሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመደወል ለማረጋጋጥ እንደተቻለው ሰራተኞቹ ወደ ጁባና ሌላዋ የደቡብ ሱዳን ከተማ ወደሆነቸው ማላካ ምንም አይነት ትኬት እንዳይቆርጡ፣  ትእዛዝ ተላልፎላቸዋል። ለሰራተኞቹ በምክንያትነት የተገለጸላቸው የጸጥታ ችግር የሚል ነው። አቶ መለስ አየር መንገዱ በረራ እንዲያቋርጥ ያዘዙት ፤ ሁለቱን አገሮች ለማስታረቅ መንግስታቸው የጀመረው ጥረት ሊሳካ አለመቻሉ ስላበሳጫው ነው የሚሉ ወገኖችም አሉ። አቶ መለስ የደቡብ ሱዳን ባለስልጣናትን ዘልፈዋቸው እንደነበር የዲፕሎማቲክ ምንጮችን ዋቢ በማድረግ መዘገባችን ይታወሳል።

የደቡብ ሱዳን መንግስት አየር መንገዱ በረራውን በማቋረጡ ለኢትዮጵያ መንግስት አቤቱታ አቅርቧል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ካርቱም የሚያደርገውን በረራ ሳይሰርዝ ወደ ጁባ የሚያድረገውን በረራ መሰረዙ ፖለቲካዊ ተቀባይነት አይኖረውም ብሎአል። አቶ መለስ በግልጽ የአልበሽር ደጋፊ ሆነው መውጣታቸው እየተነገረ ነው። ከደቡብ ሱዳን መንግስት ጋር የሚፋለመውን የደቡብ ሱዳን አማጽያንንም እንደሚረዳ ሚስጢራዊ መረጃዎች አመልክተዋል። ጄኔራል አልበሸር ጦራቸው ጁባ ድረስ በመሄድ ደቡብ ሱዳንን የሚያስተዳድረውን የኤስ ፒ ኤል ኤም አመራሮችን ከስልጣን እንደሚያወርዱ ዝተዋል። በሌላ ዜና ደግሞ ካፒታል ኤኢ.ኤም እንደዘገበው፤ የሱዳን መንግሥት ዜጎቹ ከደቡብ ሱዳን ጋር ለሚደረገው ጠቅላላ ጦርነት እንደሚመለመሉ አስታውቋል ::

በኬንያ የሱዳን አምባሳደር ከማል እስማኤል ሰዒድን ዋቢ ያደረገው ይኸው የ ካፒታል ኤፍ. ኤም ዘገባ፣ በነዳጅ ዘይት ምክንያት በተባባሰው ውጥረት ምክንያት የደቡብ ሱዳን ወታደሮች ከአካባቢው ካልወጡ፤ የአልበሽር መንግስት ማናቸውንም ዓይነት ዋጋ ከፍሎ ጦርነት የመጀመር አቋም ላይ ደርሷል::“እንደ ነፃ አገር ሱዳን ራሷን መከላከል ትችላለች” ያሉት አምባሳደር ከማል፤ “ጦርነት ከተጀመረም ጠቅላላ ሕዝቡ እስከመጨረሻው ይዋጋል” ሲሉ ተደምጠዋል:: “ይህ የመደበኛው ሠራዊት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ በሁሉም የሙያ መስኮች የተሰማሩ ዜጎች ጉዳይ ነው።

 ስለሆነም ፤ሁሉም ሱዳናውያን በውጊያው ላይ ይሰለፋሉ” በማለት መንግስታቸው የቀድሞ አካሉ በነበረችው በጁባ ላይ ሁሉን አቀፍ ክተት ለማወጅ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታውቀዋል-አምባሳደር ከማል። አክለውም፦” አገራችን ወደ ጦርነት ለመግባት ፍራቻ የላትም !ደቡብ ሱዳኖች ከአወዛጋቢው ስፍራ እስኪወጡ ድረስም ውጊያው ይቀጥላል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል::የነዳጅ ዘይት  እምብርት ተብላ በምትጠራው “ሔግሊግ” ከተማ ባለፈው ቅዳሜ የሱዳን አየር ኃይል በፈጸመው ድብደባ ከፍተኛ ውድመት መድረሱን ዓለማቀፍ ብዙሀን መገናኛዎች ዘግበዋል::

አይ ኤም ኤፍ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገት አሀዝ ከግማሽ በላይ አወረደው

ኢሳት ዜና:-
የአለም የገንዘብ ተቋም በመህጻረ ቃሉ አይኤም ኤፍ ኢትዮጵያ በያዝነው አመት 5 በመቶ እድገት እንደምታስመዘገብ ሲገልጽ፣ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ከኢትዮጵያ የተሻለ እድገት እንደሚያስመዘግቡ ገልጧል። ምንም እንኳ አቶ መለስ በፓርላማ ንግግር ታሪካቸው ተገኝተው ለመጀመሪያ ጊዜ የዚህን አመት የኢትዮጵያ እድገት ሳይናገሩ ቢወጡም፣ የመንግስቱ መገናኛ ብዙሀን ግን አሁንም ኢትዮጵያ 11 በመቶ እድገት በማስመዝገብ፣ በአፍሪካ ፈጣን እድገት ያስመዘገበች ብቸኛ አገር እንደሆነች አድርገው ፕሮፓጋንዳ መስራታቸውን ቀጥለዋል። አይ ኤም ኤፍ በዚህ ሳምንት ባወጣው ሪፖርት የኢትዮጵያ የዚህ አመት እድገት 5 በመቶ ይሆናል ብሎአል።

አይ ኤም ኤፍ ያወጣው ሪፖርት የመለስ መንግስት የዘንድሮውን ጨምሮ በሚቀጥሉት 5 አመታት አስመዘግበዋለሁ ከሚለው ከ11 እስከ 14 በመቶ ጋር ሲነጻጸር ከግማሽም በታች ነው። የአቶ መለስ መንግስት የትራንስፎርሜሽን እቅድ አገሪቱ በሚቀጥሉት አምስት አመታት 14 በመቶ እድገት እንደምታስመዘግብ ይተነብያል። እንደ አይ ኤም ኤፍ ሪፖርት ከ5 በመቶ በላይ የኢኮኖሚ እድገት ያሚያመዘግቡት አገሮች ናይጀሪያ፣ አንጎላ፣ ጋቦን፣ ጃድ፣ ጋና ፣ ኮትዲቫር እና ቻድ፣ ታንዛኒያ፣ ኮንጎና ሞዛምቢክ ናቸው።


Media Control In Ethiopia

By Graham Peebles 

Activists head for NY
Human rights activists pose for a group picture before heading for New York to protest against Meles Zenawi at Columbia University in New York (Photo: courtesy of Tewodros Mekebeb; Sept 22, 2010)
Activists head for NY
Activists on one of the buses heading for New York's Columbia University to protest against the presence of Ethiopia's dictator, Meles Zenawi (Photo: courtesy of Abebe Belew; Sept 22, 2010)
Democracy sits firmly upon principles of freedom, justice, social inclusion and participation in civil society. Where these qualities of fairness are absent so too is democracy, for the word is not the thing, to speak of democratic values is easy enough, to dismantle repressive methods and State practices that deny there expression is quite another. President Meles Zenawi Asres of Ethiopia knows little of democracy, human rights or the manifestation of democratic principles and much of repression and intimidation.

 The EPRDF government rules Ethiopia with a heavy hand of control, restricting completely free assemble– a universal right written into the Universal Declaration of Human Rights (UDHR), inhibiting the freedom of the media and denying the people of Ethiopia freedom of expression in manifold ways.

Media freedom is a basic pillar of any democratic society. Freedom of political expression, freedom of speech, and freedom of the press are essential elements of a democracy. Whilst media independence throughout the world is contentious at best, autonomy from direct State ownership and influence is a crucial element in establishing an independent media.

The Ethiopian State owns and strictly controls the primary media of television and radio. Not only is there no independent TV and radio in Ethiopia, but access to information is also tightly controlled, as Human Rights Watch (HRW) makes clear in its report, One Hundred Ways of Putting Pressure. Violations of Freedom of Expression and Association in Ethiopia, “the independent media has struggled to establish itself in the face of constant government hostility and an inability to access information from government officials.” Since the 2005 elections in Ethiopia the government has systematically introduced tighter and tighter methods of  control, HRW continues, over the past five years the Ethiopian government has restricted political space for the opposition, stifled independent civil society, and intensified control of the media.

Owning information

Since the end of the civil war in 1991 privately owned newspapers and magazines have been appearing and despite heavy regulation by the Meles government, this area of Ethiopian media is expanding. This the government reluctantly tolerates, knowing that print media is of little significance, due to low literacy of the adult population (48%), a shameful figure that the EPRDF is no doubt delighted with, high levels of poverty and poor infrastructure making distribution difficult, newspapers are not widely circulated or read, consequently the main source of information for the majority of people is the state owned television and radio, which serve as little more than a mouthpiece of propaganda for the resident regime, the EPRDF. Internet media is also restricted, with access to the web the lowest in Africa; Research & Markets found “Ethiopia has the lowest overall teledensity in Africa.

The population is approaching 90 million, but there are less than 1 million fixed lines in service, and a little more than 3.3 million mobile subscribers. The number of internet users is dismal – below 500,000 at the end of 2009.” 1 The World Bank puts the figure a little higher at 7.5% of the population. In another demonstration of democratic duplicity, the government of Ethiopia controls all telecommunications. Internet and telephone systems must run through the State owned Ethiopian Telecommunications Corporation. The vast majority of the population – 82.40% in 2010, according to a World Bank report released in 20112, live in rural areas and have no access to the ‘worldwide web’ at all. By maintaining monopoly control of telecommunications the Ethiopian Government is denying the majority of the population access to another key area of mass information.

This is an additional infringement of basic democratic principles of diversity and social participation, as Noam Chomsky makes clear “The most effective way to restrict democracy is to transfer decision-making from the public arena to unaccountable institutions: kings and princes, priestly castes, military juntas, party dictatorships, or modern corporations.”3 Party dictatorships fits the Ethiopian government tailor-made, although their arrogance and vanity would no doubt prefer the title of ‘kings and princes’, Emperor Meles perhaps, following in the brutal glow of that other conceited controller Halie Sellassie. The EPRDF regime is in fact a dictatorship and known as such to the majority of Ethiopians living inside and indeed outside the country, who are courageous enough to speak out and make their views known. Courageous indeed, for as with all cowardly brutal states, the EPRDF rules by violence, intimidation and fear, HRW again Ethiopia’s citizens are unable to speak freely, organize political activities, and challenge their government’s policies through peaceful protest, voting, or publishing their views without fear of reprisal. Such is democratic living under the Meles machine.

Law Breakers  
Freedom of thought, freedom of expression and of information is a basic requirement under the UDHR. Article 19 makes this clear “Everyone has the right to freedom of opinion and expression; this right includes freedom to hold opinions without interference and to seek, receive and impart information and ideas through any media and regardless of frontiers.” Although the UDHR is not in itself a legally binding document, it provides moral guidance for states and offers a clear indication of what we as a world community have agreed as the basic requirements of correct governance and civilized living. In the preamble is stated “it is essential, if man is not to be compelled to have recourse, as a last resort, to rebellion against tyranny and oppression, that human rights should be protected by the rule of law.” Tyranny and oppression is the cloud under which the good people of Ethiopia are living and have lived for the twenty-year rule of President Meles and co. 

It is through the implementation and enforcement of international law, established to safeguard the people’s basic human rights that the suffering and injustices may and will be brought to an end. The sister document to the UDHR the International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR) provides such legal protection and is indeed legally binding. There we find, Article 19, paragraph 1 ” Everyone shall have the right to hold opinions without interference.” And paragraph 2 “ Everyone shall have the right to freedom of expression; this right shall include freedom to seek, receive and impart information and ideas of all kinds, regardless of frontiers, either orally, in writing or in print, in the form of art, or through any other media of his choice.”

Ethiopia ratified this international treatise on 11th June 1993, and is therefore legally bound by its articles. By imposing tight regulatory controls on media inside and indeed outside of Ethiopia, the case of ESAT TV based in Holland, whose satellite signal is repeatedly [illegally} blocked by the EPRDF, is an important case in question. Not only is the Ethiopian government in violation of international law, but by completely restricting the freedom of the media and inhibiting completely any hint of dissent, the regime is also in contradiction of its own constitution.

Article 29, entitled rather optimistically ‘Right of Thought, Opinion and Expression’ states, 1. Everyone has the right to hold opinions without interference. 2. Everyone has the right to freedom of expression without any interference. This right shall include freedom to seek, receive and impart information and ideas of all kinds, regardless of frontiers, either orally, in writing or in print, in the form of art, or through any media of his choice. 3. Freedom of the press and other mass media and freedom of artistic creativity is guaranteed. Freedom of the press shall specifically include the following elements: (a) Prohibition of any form of censorship. (b) Access to information of public interest.4 Clear and noble words, indeed democratic in content and tone, however words that sit filed neatly upon the shelf of neglect and indifference, as the people suffer and cry out to their mother country, serve only as a mask of convenience and deceit allowing the betrayal of the many to continue. Human Rights Watch gently states, the 1995 constitution incorporates a wide range of human rights standards, and government officials frequently voice the state’s commitment to meeting its human rights obligations. But these steps while important, have not ensured that Ethiopia’s citizens are able to enjoy their fundamental rights.

State suppression

In 2009 the EPRDF passed two inhibiting pieces of legislation that embody some of the worst aspects of the governments decent towards greater repression and political intolerance. The controversial CSO law, is according to HRW, one of the most restrictive of its kind, and its provisions will make most independent human rights work impossible. A ‘counterterrorism’ law was introduced at the same time; this second piece of repressive legislation allows the government and security forces to prosecute political protesters and non-violent expressions of dissent as terrorism. Since the introduction of these internationally criticised laws, the UN Jubilee Campaign in its report ‘Human Rights Council Universal Periodic Review Ethiopia’ recommends the adoption of this law [emphasis mine] be repealed,” the umbrella term ‘terrorist’, meaning anyone who disagrees with the party/state line continues to be used and manipulated as justification for all manner of human rights violations and methods of suppression and control – the aim of all dictatorships.

What defines a terrorist or an act of terrorism remains vague and ambiguous, enabling the Meles regime to construct definitions that suit them at any given time. Amongst other travesties of justice the legislation, The Bureau of Investigative Journalism reveals, “permits a clamp down on political dissent, including political demonstrations and public criticisms of government policy, it also deprives defendants of the right to be presumed innocent.“5 A primary function of the media in a democratic society is to examine and criticise the government and provide a public platform for debate and participation. This law denies such interaction and freedom of expression. The law is in violation of the ICCPR and blatantly contravenes the much-championed Ethiopian constitution; idealised images of goodness, remaining un-manifest, stillborn.

The anti-terror law is a pseudonym for a law of repression and control, made and enforced by a paranoid regime, that is determined to use all means in its armoury to quash any dissent and maintain a system of disinformation and duplicity. Media organisations that disagree with the EPRDF party line run the risk of being branded, under this law ‘terrorists’, arrested and imprisoned as such. Dawit Kebede, editor-in-chief of Awramba Times, says “the law provides a pretext for the government to intimidate and even arrest journalists who fall afoul of its wording. Kebede said the regulations were a government campaign to oppress all forms of dissident activity.” (Ibid) This new unjust law completely inhibits ability of the media to report anything that is deemed critical of the current government. All opposing voices to policy are stifled; journalists are frightened and the facility to expose and criticize the many serious violations of human rights, to provide a balanced view of the issues facing the country are denied. The rights to freedom of expression and association are completely restricted, all independent voices have been virtually silenced and freedom of speech and opinion are denied. Human Rights Watch makes clear its concern, over the past five years the Ethiopian government has restricted political space for the opposition, stifled independent civil society, and intensified control of the media.6

Control flows from fear, the greater the dishonesty, corruption and greed the more extreme the controls become. Under the neglectful corrupt governance of the EPRDF, Ethiopians are subjected to a range of human rights abuses and violations political opposition has been unofficially banned, making this democracy sitting in the Horn of Africa a single party dictatorship. The UN in its human rights report finds, “resistance to opposition has become the primary source of concern regarding the future of human rights in Ethiopia” and confirms the view of HRW, stating “The CSO law directly inhibits rights to association, assembly and free expression.” The Meles regime seek, as all isolated corrupt dictatorships do, to centralize power, deny dissent and freedom of expression and suppress the people by intimidation, violence and fear. Creating an atmosphere of apprehension, extinguishing all hope of justice, true human development and freedom from tyranny. Disempowerment is the aim, the means are well known, crude and unimaginative, keep the people uneducated, deny them access to information, restrict their freedom of association and expression and keep them entrapped.

Demanding justice

The downtrodden suppressed people of Ethiopia, living under the brutality of the Meles regime, whose human rights are being ignored, without an effective media, have no voice. The controls that deny media freedom and the people the freedom of association and expression, guaranteed under the Ethiopian constitution and international law, must be repealed, HRW in its detailed report makes a series of basic demands of the Ethiopian government, which reinforce this, key among them is the call to “Guarantee unrestricted access to Ethiopia to international media and independent human rights investigators, and cease harassment of Ethiopian media.”

The days of the dictator are over, no amount of repressive legislation can any longer safeguard a regime that rules through violence and inhibition. Meles and his cronies ensconced behind armed walls of duplicity, may well seek control, the fearful always do, the will of the people though is for freedom, justice and peace, enjoy your privilege President Meles, for your days are numbered, the will of the people must and shall be done for justice and the rule of law underlies their every call for liberty and the observation of their human rights. 

Notes:
1.http://www.newsdire.com/news/730-the-number-of-internet-users-in-ethiopia-will-jump-to-12-million.html

2. http://www.tradingeconomics.com/ethiopia/rural-population-percent-of-total-population-wb-data.html
3. Domestic Constituencies Noam Chomsky. http://www.chomsky.info/articles/199805–.htm
4. Constitution of The Federal Democratic Republic of Ethiopia. www.africanlegislaturesproject.org/…/Constitution%20Ethiopia.pdf
5. The bureau of investigative journalism
http://www.thebureauinvestigates.com/2011/09/29/ethiopian-media-gagged-by-anti-terror-laws
6. Human Rights watch (HRW) http://www.hrw.org/en/reports/2010/03/24/one-hundred-ways-putting-pressure-0


 


Thursday, April 19, 2012

አማራ ማነው?

ባጠቃላይ ይህን አስመልክቶ ጥናት ማድረግ ከፈለጋችሁ መርድ ወ/አረጋይ፣ አስመሮም ለገሰ፣ አንቷን ዳባዲ ኤ.ትሪዩልዚ ያቀረቧቸውን የታሪክ ትንተናዎች ከነጋሶ ጊዳዶ፣ መሀመድ ሀሰንና ሌሎቹም ብሔረተኞች ከፃፏቸው ጋር ማወዳደርና የግላችሁን ማጠቃለያ መስጠት ትችላላችሁ። (በተጨማሪ በዚህ ፅሁፍ ተጠቃሽ የሆኑትን ምንጮችና ሌሎችንም ታሪካዊ ማስረጃዎች ማገናዘቡ ጠቃሚ ነው).
Oromo migration in the 6th century 


አማራን በተመለከተ ሁላችሁም እንደምታውቁት ሕወሀት ማዕከላዊ የፖለቲካ ስልጣን ሲጨብጥ ፀረ-አማራ አቋም ባደባባይ በማናፈስ የተቀሩትን ብሔሮች ከጎኑ በማሰለፍና አማራውን በማስመታት ለአገዛዙ ጠንካራ መሰረት ለመጣል ችሏል። በዚህ አንገፍጋፊ የዘር ማጥፋት ወንጀል በተፈፀመበት ወቅት የሁኔታዎቹ አካሄድ ወደ እርስ በርስ ጦርነት አምርቶ ውጥንቅጥ ውሰጥ ላለመግባት መአሕድ ተቋቋመ። ይህ ክስተት በቴሌቭዥን በመለሰ ዜናዊ፣ በፕሮፌሰር መስፍንና በሌሎች መካከል የአማራ ብሔረሰብ አለ ወይም የለም የሚል እሰጣ ገባ አስከትሎ ነበር። ፕሮፌሰሩ “አማራ ብሔረሰብ ሳይሆን አማርኛ ተናጋሪ አለ” ብለው መደምደማቸውን ማንም አይረሳውም። ይህ አባባል በውቅቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ቆሽት አንድዷል። በዘር ላይ የተመረኮዘ አላማ ለሚያራምዱ ድርጅቶችና ብሔረተኛ ተራኪዎቻቸው ግን አባባሉ አስፈንጥዟቸዋል። ነገር ግን እነዚህ ቡድኖች ራሳቸው “መመሪያ” ብለው ያተሟቸውን ሰነዶች መለስ ብለው በክርክሩ ወቅት መመልከት ተስኗቸዋል።

              South-east Ethiopia c 1500
ኢትዮጵያን በተመለከተ የተለያየ አቀራረብና ትንታኔ አንዲሁም አቋሞችን ያነገቡ ቁጥር ስፍር የሌላቸው የታሪክ መፅሀፎችና ጥናታዊ ፅሁፎች አሉ። የዚህ አጭር መጣጥፍ ዋነኛ ትኩረት የኦሮሞ ወረራና ተስፋፊ ብሔረተኛ ትንተናዎች ከታሪክ ማስረጃ አኳያ እንዴት ይገመገማሉ የሚለው ላይ ያተኩራል።

ፀሀፊው በግልፅ ማሳወቅ የሚፈልገው ማንኛውም የሰው ልጅ ታሪክ አዎንታዊ ጎን ያለውን ያህል አሉታዊ ገፅታዎቹም ምንም ሊደብቁት ቢሞክሩም ግዜውን ጠብቆ መውጣቱ የማይቀር መሆኑን ነው። የበርካታ ኦሮሞ (ገዳዎች) ወደ ተለያዩ ኢትዮጵያ ክፍሎች በተስፋፋበትና ወረራ ባከሄዱበት ጊዜና በኋላ ለብዙ ሺህ ዓመታት በራሳቸው ቋንቋ፣ ባህልና ልምድ ይመሩ የነበሩ ብሔሮች ከአቅማቸው በላይ በሆነ ሀይል ተውጠዋል፣ አናሳ ሆነዋል እንዲሁም ከነ ጭራሹ ጠፍተዋል። እስካሁን ባነበብኩትና ባየሁት ታሪካዊ ትንተና (99 በመቶ የኦሮሞ ብሔረተኛ አቋም ላይ የሚያዘነብሉ ተራኪዎች) ሁሉም በአደባባይ ጉዳዩን በማድበስበስና (ገዳ፣ ገባሮ፣ ጉድፈቻ) ወዘተ… በሚሉ አቀራረቦች በመጠቀም መስፋፋቱን ሰላማዊ ለማስመሰልና አሉታዊ ገጽታ ለመስጠት ከመጣር አለመቆጠባቸውንና ምናልባትም “የወጋ ቢረሳን” ብቻ የመረጡና “የተወጋ አይረሳ” የሚለውን ችላ እንደሚሉት ተገንዝብያለሁ። 

ለመንደርደሪያ እንዲያግዝ በሔረተኞቹ ከሚሉት ልጀምር “ኩሾች ኑቢያ፣ ናይሎ ሰሀራን፣ ኦሞቲክን ጨምሮ የኛ ናቸው፤ ሉሲ ከኛ ዘንድ ስለተገኘች የሰው ዘር መፍለቂያም ነን፤ እርሻ በዚህ ዓለም የተጀመረው በኦሮሚያ ነው ይላሉ”። አባባሉ ትረካቸውን ገና ከመጀመሪያው በታሪክ ተመራማሪዎች በኩል ጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ያደርገዋል። “ከቋንቋና አርኪዮሎጂ ጥናቶችና ምርመራዎች በቅርብ ግዜ በተገኙት መረጃዎች መሰረት እርሻ የተጀመረው የሰሀራ በረሀ ከመከሰቱ በርካታ ክ/ዘመናት በፊት በኢትዮጵያ፣ በመካከለኛው ሱዳንና በናይጀር ነው።” ሲል Africa Emerging Civilization In Sub Sahara Africa በተባለው የፅሁፍ ክምችት ላይ ተዘግቧል። በኬንያና ኢትዮጵያ ድንበር ላይ ኦሮሞዎች በታሪክ የመጀመሪያ መኖሪያቸው እንደነበር የሚያረጋግጡና ዛሬ ኦሮሞዎች የሰፈሩባቸው አብዛኛዎቹ ግዛቶች ከሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሀይልና በወረራ የተነጠቁ ለመሆኑ በርካታ ምርምርና ጥናትን መሰረት ያደረጉ ፅሁፎች ሞልተዋል። 

የኦሮሞ ነፃ አውጪ ድርጅት በዚህ አባባል አላማውን በሚገልፀው ደበተሩ አይስማማም፣ በተጨማሪ “ሐበሻዎች በዘመናዊ የአውሮፓ መሳሪያ በመደገፍ ማሸነፍ እስከቻሉበት 19ኛው መቶ ክ/ዘ መገባደጃ ድረስ ኦሮሞ ነፃ ነበር” በሚል አቀራረብ ትግል መጀመሩን ያበስራል። በታሪክ ከብት አርብቶ አደር የነበረውንና ከደቡብ ኢትዮጵያ ተነስቶ ወደ አሁን የኦሮሞ ክልሎች ተስፋፍቶ በሌሎች ሕዝቦች መሬት ላይ ሊሰፍር እንደቻለ ያሉትን ተጨባጭ የታሪክ ሀቆችን በማዛባትና በውሸት የፈጠራ ወሬ ያልነበረና ያልተደረገ ታሪክን ከአቀንቃኞቹ ጋር በመሆን መፃፍን ገፍቶበታል። Oromo Migration & Their Impact በሚል ርዕስ የUS Library of Congress ባቀረበው ህትመት በ16ኛው መቶ ክ/ዘ አጋማሽ … ኦሮሞዎች በደቡብ ኢትዮጵያ ጫፍ ሰፍረው የነበሩና በከብት አርቢነት ላይ ተመስርተው በተለያዩ ተፎካካሪ ቡድኖች የሚተዳደሩ ነበሩ። ይህም ለጦርነት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮላቸዋል … በ1550 እ.አ.አ አካባቢ አጥፊ ወረራዎችና መስፋፋቶችን (predatory expansion) በጎረቤቶቻቸው ላይ ፈፅመዋል …” ሲል ሀቀኛውን ታሪክ ገሀድ አድርጓል። ይህም የሚያመለክተው ከ460 ዓመት በፊት የተጀመረው ወራሪና ተስፋፊ አክራሪ ብሔረተኝነት በ21ኛው ክ/ዘ መልኩን ከ(ገዳ) ወዘተ… ወደ “መገንጠል” ጥያቄ ቀይሮ በመካሄድ ላይ መሆኑን ነው። 

በመሰረቱ ዛሬ ኦሮሞ ተስፋፍቶ የያዛቸው መሬቶች ከ16 ኛው መቶ ክ/ዘ አጋማሽ በፊት አንድም ኦሮሞ ኖሮበት የማያውቅባቸው ግዛቶች በታሪክ ሀብትነታቸው የእነ ሪያ ዳሞት፣ ማኦ፣ ኮሞ፣ መዠንገር፣ ሺናሻ፣ ከፋ፣ የም፣ አማራፈተጋር፣ አርጎባ፣ ደዋሮ፣ ባሊ፣ አዳል(ሀውዳል)፣ ሀረሪ፣ ጉራጌ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ጌዲዮ፣ ሀድያ፣ ጋፋት፣ ሸካና ሌሎች ናይሎ ሰሀራዊና ኦሞቲክ ሕዝቦች ሲወርድ ሲዋረድ በቋንቋቸው፣ በባህላቸውና ልምዳቸው ተከብረው የኖሩባቸው ለመሆኑ አመላካች ታሪካዊ ማስረጃዎችን ወደ ጎን በመግፋት ሀቁ ሁሌ ተደብቆና ተድበስብሶ ይኖራል በሚል የተሳሳተ አካሄድ ብሔረተኞቹ መምረጣቸው ዞሮ ወደፊት ለነርሱም ችግር መፍጠሩን አርቀው ያስተዋሉ አይመስልም። ባሁኑ ግዜ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች ኦሮምኛ መጠሪያ ስላላቸው ቦታዎች Marco Vigano From Barara To the Indies በሚለው የአርኪዮሎጂ ጥናቱ “ሌላና ባዕድ የሆነው ባህልና ልምድ ባስከተለው ወረራ የአካባቢና ቦታዎች ስሞች ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ ተቀይረዋል …” በሚል ካቀረበው ማብራሪያ ጋር እንጂ ከብሔረተኞቹ ትረካ ጋር ማያያዙ ትክክል እንዳልሆነ መታወቅ አለበት። 

ለምሳሌ በመልካ ቁንጥሬ ያሉትን የረጅም ዘመን ያላቸው የድንጋይ ትክሎችና ታሪካዊ ቅርሶች በማንኛውም ሳይንሳዊ ስሌት ጨርሶ ከኦሮሞ ጋር ግንኙነት የላቸውም። ቦታውን ከደዋሮና ምናልባትም ከጋፋት ወይም ጉራጌ ሕዝቦች አሰፋፈር ጋር ማያያዝ ይቻላል። ምክንያቱም በዛን ግዜ ኦሮሞ ኑዋሪነቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ጫፍ ኬንያ ድንበር ላይ ብቻ ነበር። ሌላው የዛጉዌና የክርሰትያን ኢትዮጵያ ስርአት በ12ኛው ክ/ዘ ማለትም ኦሮሞ ባካባቢው መታየት ከመጀመሩ 450 ዓመት በፊት ለመኖሩ በመልካ ቁንጥሬ የአዳዲ ማሪያም ውቅር (ፍልፍል) ድንጋይ ገዳም፣ በመተሀራ የተገኙት ጥንታዊ የፈላሻ ማምለኪያዎችን ወዘተ… መጥቀሱ በቂ ይመስለኛል። 

ሌላው በኦሮሞና ሶማሌ ብሔረተኛ ተራኪዎች መሀል ያለው የአዋሽ ወንዝ አካባቢ ጥንታዊ ታሪክ ጭቅጭቅ አንዱ ራሱን የቻለ ትንተና ስለሚጠይቅ በዚህ ፅሁፍ አይቀርብም። ነገር ግን ብሔረተኞች እንደሚያነበንቡት ሳይሆን ሁለቱን በተመለከተ H.S.Lewis the origin of the Gala and Somali በሚለው ጥናቱ “በተለምዶ ጋላ በአፍሪካ ቀንድ ከሱማሌ ቀድሞ (በፊት) ሰፍሮ ነበር የሚለው አገላለፅ አሁን ተቀባይነት የለውም።” ያለውንና በርካታ የታሪክ ምሁራን በዚህ ጉዳይ ያቀረቡትን ምርምር ወደፊት በሌላ ርዕስ እመለስበታለሁ። (በጥቅሱ የቀረበው የቃላት ምርጫ የ H.S.Lewis እንጂ የእኔ አይደለም)።

አሁን ለሰለባ ትኩረት የተደረገው የመስፋፈት ጥማት በፀረ- አማራ የፕሮፓጋንዳ ስራና አመቺ ሁኔታ ከተፈጠረ አማራውን በመጨፍጨፍ ግዛቱን መቀራመት ላይ ነው። እዚህ ላይ በርካታ ምሁራንን በማቀፉ የሚወሳለት የኦሮም ድርጅት ለምን (ሐበሻዎች) የሚለውን ቃል እንደተጠቀመ ባይገባኝም አረቦች የኢትዮጵያ ሕዝቦች የተደበላለቁ ወይም የተካለሱ መሆኑን መሰረት በማድረግ የአገሪቱን ነዋሪዎች ሊገልፁ የሞከሩበት መጠሪያ ስለመሆኑ ግን አጥተውት አይመስለኝም።

ሁላችንም የምንስማማበት ጉዳይ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ብሔር ብሔረሰቦች አለማጋነን ከሁሉም በደም የተዋሀደና የተዋለደ፣ በ16ኛው ክ/ዘ አጋማሽ ጀምሮ ከደቡብ የአገሪቱ ጫፍ ተነስቶ ዛሬ በያዛቸውና በተቆጣጠራቸው ገዥ ግዛት አኳያ በቀዳሚነት የተሳካ መስፋፋት ያደረገው ኦሮሞ ቅኝ- ገዢ ብሔረሰብ እንደሆነ ነው። ዋነኛው ኦነግንና ብሔረተኛ ተራኪዎቹን የሚያስደነግጠውና ዛሬ እነርሱ ተጠናክረውና ተደራጅተው “መገንጠል” ላይ ያተኮሩትን ያህል በተራው የዛሬዎቹን ምራብና ምስራቅ ወለጋ ከሚባሉት በኦሮሞ አስከፊ ወረራና መስፋፋት የተገፋውና የተጨፈጨፈው የበርታ፣ ማኦና ሌሎችም ብሔሮች አንድ ቀን አብረው ፀረ ኦሮሞ ትግል ያነሳሉ ብለው ማሰባቸው ነው። 

ይህ አንድ ምሳሌ ሲሆን የኦሞቲክ አባልና እየነቁ ታሪካቸውን በጥልቀት በማወቅ መንቀሳቀስ የጀመሩት ከፊቾና የም ብሔረሰቦች እስከዛሬ ድረስ ሰሚ አጥተውና ተበድለው እንጂ ጂማ በሙሉ የነርሱ እንደሆነና በኦሮሞ ሰለባ ታሪካዊ ግዛታቸውን ስለመነጠቃቸው ድምፃቸውን በአደባባይ ከማሰማት ከንጉሡ ጊዜ ጀምሮ ቦዝነው አያውቁም። መዠንግሮችና ሸካም ብሔረሰቦችም ዛሬ ኢሉባቦር በሚባለውም ቦታ ላይ ተመሳሳይ አቋም አላቸው። በባሌና ሀረር ደግሞ ሱማሌዎች ኦነግን የሚያስበረግግ የይገባኛል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን ከብሔረተኛ ኦሮሞዎች ጋር በየአጋጣሚው ግጭቶችን ከማድረግ ያልተቆጠቡና ወደፊትም ፍጥጫው ቀጣይነቱ ጥርጥር የለውም።

 በኦሮሞ ወረራ ዘመን ዳር ድንበራቸውን የተነጠቁት ዛሬ አናሳ የሆኑት ብሔሮች በፖለቲካ ንቃት እየጎለበቱ በሄዱ ቁጥርና የዘመኑ ስልጣኔ ተቋዳሽ አካል መሆን በመጀመራቸው ኦነግ በፃፈው የሀሰት ታሪክና ድርጅታዊ አቋም ተከታይ አክራሪ ብሔረተኞቹ ራሳቸው በከፈቱት በር ኦሞቲኮቹና ናይሎ ሳሀራዎች ሰተት ብለው በመግባት የነፃነት አቋም ያነገበ ትግል በመጀመር ኦሮሞዎቹን ወደ መጣችሁበት ተመለሱ ማለታቸው የማይቀረር የወደፊት የታሪክ ሀቅ ነው። ሌሎችም በየተራ ይነሳሉ። ለኦሮሞ ነፃ አውጪ ቡድንና ብሔረተኞችም ጉዱ እንደ ጭራ ከበስተኋላ የሚሆንባቸው ግዜ በህይወት ዘመናቸው በነበልባል እሳት እንደሚያቃጥላቸው ጥርጥር የለኝም። 

ለምሳሌ Alfredo Gonzales ና Victor Fernandez በቤኒሻንጉል ሕዝቦች ታሪክና ባህል ላይ ባቀረቡት ፅሁፍ “በ1988 (እ.አ.አ) በአሶሳ የተገንጣዩ ኦሮሞ ቡድን ታጣቂዎች በብዙ መቶ የሚቆጠሩ አማራዎችን ሲገሉ የበርታ ተወላጆችን ጥቁር ኦሮሞ ነን እንዲሉ ሲያስገድዱ በርታዎች እምቢ በማለታቸው በሁለቱ መካከል ግጭት ተፈጥሯል” ። ይህ ጉዳይ አሁን ስር እየሰደደ በመሄድ ላይ ሲሆን በቅርቡ በቤኒሻንጉልና ኦሮሞ ክልል ፖሊሶችና ሕዝባዊ ሰራዊት መካከል ተከስቶ የነበረውን ፀብ(ጠብ) ለማርገብ የፌደራል ጉዳይ ሚኒስትሩ ከቦታው ለማስታረቅ ሄዶ እንደነበር በዜና መነገሩ ተደምጧል (2004 ዓ/ም ጥቅምትና/ህዳር)።

እስቲ በተራ ከፍ ሲል የተቀመጠውን አባባል ከታሪክ አኳያ እንመርምር። ኩሽ ማነው ወይም እነማን ናቸው? በአመዛኙ ታሪክ የሚያስተምረው ጥቁር ቆዳ ያለው ሕዝብ በአፍሪካ የተባዛው ከክ/ዓለሙ በስተምራብ ተነስተው በተስፋፉ (ባንቱዎችና) ከሰሜን ምስራቅ ወደ ምስራቅ በደቡብ አቅጣጫ በተስፋፉት (ኩሾች) እንደሆነ ነው። በመፅሀፍ ቅዱስ ስላለው ዊኪፒድያ ሲያትት “ኩሽ … የሀም መጀመሪያ ልጅና የኩሽ ሕዝቦች አባት እንደሆነ ይገመታል። እነርሱም ጠይም የቆዳ ቀለም ያለቸውና በጊዮን ወንዝ አካባቢ በጥንቱ ግምት በምድረ አረብያና አትዮጵያ የሚኖሩ ናቸው” ይላል። ይሄው የመረጃ ምንጭ “ኩሽ የሚለው መጠሪያ የመጣው ከምድረ ኩሽ ማለትም (ከዛሬዋ ሱዳንና ከደቡባዊ ግብፅ ከመጣ ጥንታዊ የጎሳ ቡድን) ሲሆን ሁኔታውን ሌሎች ምሁራን ከኢትዮጵያ አይሁዶች ወይም “ቤተ እስራኤሎች” ጋር እንደሚያያይዙት ይጠቁማል። 

በዚህ ጉዳይ የእስራኤላዊያን ዲያስፖራ ክፍል አንድና ሁለትን ለበለጠ መረጃ መመልከት ይረዳል። ባጭሩ ካገላበጥኳቸው መረጃዎች መረዳት የቻልኩት ኩሽ በዛሬዎቹ ሱዳን (ሰሜንና ሰሜን ምስራቅ)፣ በኢትየጵያ ሰሜናዊና ምእራባዊ (በጥቂቱ) ፣ በደቡባዊና ምስራቃዊ (በአመዛኙ)፣ በሶማሊያ፣ በጅቡቲ፣ በሩዋንዳ፣ በታንዛንያ እንዲሁም በአነሰተኛ ቁጥር በኬንያና ዩጋንዳ ይገኛሉ። በኢትዮጵያ ብቻ ሲዳማ፣ ጌዲዮ(ኦ)፣ ኮንሶ፣ ከምባታ፣ ሀዲያ፣ ኢሳና ሌሎች በኦጋዴን ያሉ ጎሳዎች፣ አፋር፣ ኦሮሞ፣ ቤጃ አማራ ወዘተ. ይገኙበታል። 

አማራውን በተመለከተ ከሌሎቹ የሚለየው ሴማዊ ቋንቋ ተናጋሪ መሆኑና አንዳንድ ምሁራን ከአረቢያ በአዱሊስ በኩል ፈልሰው በመምጣት የሰሜኑን ሕዝቦች ከአክሱም ቀደም ብሎና ከዛም በኋላ በደም፣ በባህልና ቋንቋ ስለበረዙት ዛሬ በሀማሴን፣ አካለጉዛይ ሰራዬና በትግራይ ትግሪኛ ተናጋሪዎች ጋር ክርስትናን ተቀብሎ በመግፋቱ፤ በተጨማሪም በ13ኛው መቶ ክ/ዘ ለመጀመሪያ ስልጣን ላይ ሲመጣ እንደ ኢዛና ተከታዮች (ዘዕምነገደ ይሁዳ) ብሎ በማወጁ እንጂ ሀቀኛ የዘር ግንዱንና በአፍሪካ ቀንድ ከጥንት ጀምሮ ራሱን ችሎ ሰፊ ግዛት ላይ መኖሩን በተለያዩ ሰበቦች በመካድ የፈጠሩት የውሸት ትንተና መሆኑን ታሪካዊ ማስረጃን መሰረት አድርጌ በሌላ ገፅ እመለስበታለሁ።

የአባይ ሰሀራዊዎች (ናይሎ ሰሀራን) እነማን ናቸው? በዚህ ምድብ ያሉት ብሔሮችና ቋንቋዎች በጣም በርካታ ሲሆኑ የሚኖሩትም በምስራቃዊ ሰሃራ፣ በላይኛው የአባይ ተፋሰስ፣ አልፎ አልፎም በቻድና ናይጄሪያ ጭምር በሰፊ ቦታ ላይ ነው። በኢትዮጵያና ሱዳን እንዲሁም በኤርትራ ከሚገኙት መካከል በርታ፣ ማኦ፣ ጉሙዝ፣ ሻኬቾ፣ ኑዌር አኝዋክ፣ መዠንገር፣ ናራ፣ ኩናማ፣ ዲንቃ፣ ባሪ፣ ጎባቶ፣ ወዘተ. ሲጠቀሱ ታዋቂው የኬንያ ማሳይም የዚሁ ግንድ አካል ነው። በተለይም በሱዳን የጠረፍ አካባቢዎች ይበልጡኑ ከጥቁር አባይ ሸለቆ በስተደቡብ ወለጋንና ኢሊባቦርን አካቶ ከእናሪያ ይባል ከነበረው በቀር በመዠንገር፣ በበርታ፣ በማኦና ሌሎች ብሔሮች ለብዙ ሺህ ዓመታት ይኖሩ እንደነበር ታሪክ በማስረጃ ያመለክታል። በዚህ ነጥብ ወደ ኋላ እመለስበታለሁ። 

በጎጃም ደግሞ በመተከል ጉሙዞች ድሮ ዳሞት ከሚባሉት የዛሬዎቹ ጎጃሞች ጋር ኩታ ገጠም ሆነው በጎንደር ቋራ ወረዳ ካሉት ቀበሌዎች ደግሞ ባንዱ ይኖራሉ። የኦሮሞ አነሳስ መቼና እንዴት ነበር? በዚህ ጉዳይ መላው የታሪክ ተመራማሪ የተቀራረበ አመለካከት ወስደዋል። በመጀመሪያ ኦሮሞዎች ሰፍረው የኖሩት በደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ ጫፍ በኬንያ ድንበር ብቻ ሲሆን ከብት አርብቶ አደሮች እንደነበሩም ታውቋል። ለምሳሌም እንዲረዳ በቤትዝዌል (አፍሪካ ከ16ኛ-18ኛ ክ/ዘ) በተባለ መፅሀፍ ላይ ያለውንና ደቡብ ኢትዮጵያን አመላካች ካርታ ይመልከቱ።

በተለይም ከግራኝ አህመድ ወረራ በኋላ የአገሪቱ ክርስትና እንዲሁም ተቀናቃኛቸው እስልምና አስፋፊ ወገኖች በመዳከማቸው የተለያዩ የኦሮሞ ጎሳዎች በደቡብ፣ በመሀል፣ በምዕራብና ሰሜን ከፍተኛ ቦታዎች የ(ገዳ) ስርዓት በፈጠረላቸው የጦረኝነት ባህል ከአስራ ስድሰተኛው ክ/ዘ አገማሽ ጀምሮ በባሌ፣ በደዋሮ (ከዳውሮ ይለያል)፣ በፈተጋር፣ በሲዳማ (ሙሉ ለሙሉ ያልተሳካ)፣ በአማራ፣ በአዳልና አዋሽ(ኀዋስ) ፣ በአርጎባ፣ በደቡብ፣ በበርታ፣ በማኦ፣ በዳሞት፣ በመዠንገር፣ በኢሳ ሕዝቦች ላይ አስከፊ የሆነ ጭፍጨፋና ወረራ በማካሄድ ቋንቋቸውንና ልምዳቸውን በጉልበት አስፋፍተዋል።

 ከብሔረተኞቹ በኩል ለምሳሌ ሞሀመድ ሀሰንና ተሰማ ተአ(ጠአ) ይሄን አስመልክቶ አሮሞው በወረራቸው ሕዝቦች በኩል (ተሸናፊዎቹ) በደስታና በሰላም በኦሮሞ ባህልና ቋንቋ መዋጥን (assimilation) ተቀብለዋል ይሉናል። በወራሪና በተወረሪ፣ በገዳይና በተገዳይ፣ አገርንና ሀብትን በሚቀማና በተቀሚ፣ በአጥፊና በጠፊ መካከል መቼ ነበረ ይህ አይን ያወጣ ቅዠት በታሪክ ተመዝግቦ የተገኘው? ስለ (ገዳ) ብዙ ተብሏል። እውነትው ግን ገዳ ገባርነትን ከነቃሉ ጭምር በኢትዮጵያ ያስተዋወቀ በወራሪ ጦር የማዕከላዊ እዝ አመራር ሆኖ ለብሔረሰቡ የተሳካ መስፋፋት ሚና የተጫወተ ከቅኝ ገዢዎች ዋነኛ ስልት ጋር በሚወዳደር ደረጃ በሕዝቦች ላይ ሰለባና ጥፋት ያስከተለ ክስተት ነው። 

ምንም እንኳን በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ በዚህ ፅሁፍ የተጠቀሱት ብሔረተኛ የኦሮሞ ታሪክ ተራኪዎች ሳይቀሩ በትንተናዎቻቸው በማያሻማ ሁኔታ በተለያዩ አቅጣጫዎች የተደረጉትን ወረራዎች ለምሳሌ (የሀርሙፋ ገዳ፣ የሮበሌ ገዳ፣ ወዘተ…) በሚል ገለጻ ማቅረባቸው የስርአቱን (ገዳ) አሉታዊ ጎኖች ራሳቸው ሳያስቡት መስክረዋል። በናይሎ ሰሀራዊ በርታዎች፣ በማኦና መዠንገር ላይ የሜጫ (ገዳ) ኦሮሞ ባደረሱት ጭፍጨፋ የተረፉት ሸሽተው ካገራቸው ማለትም ዛሬ ወለጋና ኢሉባቦር ከተባሉት በመሰደድ ሱዳን ድንበር ስር ተወስነው በአናሳነት እሰካሁን ድረስ የመኖራቸውን ሀቅን ኦነግም ሆነ ፀሀፊ ብሔረተኞች ደብቆ መኖርን መርጠዋል። 

ትሪዩልዚ በዚህ ጉዳይ ኮፒቶፍን ጠቅሶ ሲፅፍ “በጦርነት የተሸነፉትን ሕዝቦች ወደ ኦሮሞነት ለመዋጥ የተወሰደው ዕርምጃ ፖለቲካዊ አቋምንና ወታደራዊ ሀይልን የተደገፈ እንጂ ሰላማዊ አልነበረም። በትክክል የተደረገው ተሸናፊዎቹን … ናይሎ ሰሀራዊያንን ደረጃ በደረጃ መተዳደሪያ ከሆነው መሬታቸው በሜጫ ሰፋሪዎች መፈንገል ነው። ባሁኑ ግዜ ይህንን የተወሳሰበና አስከፊ ክስተትን ገዳን ምን ያህል (ዲሞክራሲያዊ) ወይም (መደብ አልባ) ሰርዓት ነው በማለት ለመደባበቅ (ለመሸፈን) የሚደረገው ጥረት አይረዳም። ያለፈውን ታሪክ ለማጣራትና እውነቱን ለመገንዘብ ጉዳዩን እንደገና ማጥናት (መጎብኘት) እንጂ ፈጠራና ውሸት ላይ በተመረኮዘ ትረካ (mythologizing) ማድረግ አይገባም።” 

እኔ ግን ላስታውሳቸው እሻለሁ። ለምሳሌ ሕወሀት “ትግሪኛ ተናጋሪ ሁሉ ትግሬ ነው” ኦነግም “ኦሮምኛ ተናግሪ ሁሉ ኦሮም ነው” ሌሎቹም በተመሳሳይ ሁኔታ እንወክለዋለን ስለሚሉት ሕዝብ እንድዚህ በማለት አውጀዋል። የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ግን ስሜታዊነትን ወደ ጎን በማድረግ ሰውዬው (ፕሮፌሰሩ) ለምን በራሳቸው ታሪክ እንኮፍ ለመትከል እንደወሰኑ የሚከተለውን እንዲፅፍ አነሳስቶታል። ፕሮፌሰሩ በክርክሩ ላይ በበኩላቸው የነዚህን ሀይሎች ወንጌል በመጥቀስ ለማስተላለፍ የሞከሩት መልእክት በተዘዋዋሪ “አማርኛ ተናጋሪ ሁሉ አማራ ነው” ብለው ለማስቀመጥ የሞከሩት ልክ እንደ ተቀሩት ጎጠኞች “አማርኛ” የሚናገር ኢትዮጵያዊን ሁሉ አማራ ነው ወደሚል አቀራረብ ለማመልከት እንጂ “አማራ የሚባል ብሔረሰብ የለም” ለማለት ፈልገው የወሰዱት ግላዊ አቋማቸው አይመስለኝም። 

እዚህ ላይ አንባቢ የራሱ አመለካከት እንዳለው ይገባኛል። ተከራካሪዎቹን ለስማ አባባላቸው በግዜው ግልፅ ባይሆንም አመለካከታቸው ግን ፕሮፌሰሩን ጨምሮ በተመሳሳይ “አንድ ቋንቋ የሚናገር ሕዝብ ትግሪኛ ትግሬ፣ ኦሮምኛ ኦሮሞ፣ አማርኛ አማራ ነው ወዘተ…” የሚል ስለነበር “ከዝንጀሮ ቆንጆ ምን ይመራርጡ” እንደሚባለው ተከራካሪዎቹ በሙሉ በብሔረተኝነት አመለካከታቸው አንዱ ካንዱ የሚተናነሱ ሆነው አላገኘኋቸውም። የአማራ ታሪካዊ አመጣጥ፣ የአማራ ሕዝብና ቋንቋ እንዲሁም መሰረታዊ ግዛቶቹ በጌምድርና ሰሜን ጎጃም፣ አንጎት(ያሁኑ ወሎ)ና ሸዋ መሆናቸው በተጨባጭ ታሪካዊ ጥናቶችና ማስረጃዎች ተረጋግጧል። 

ይህ ማለት ደግሞ አማራው በግዛቱ ሁሌ ቀዳሚውን ሚና ይጫወት እንዳልነበርም ግልፅ ነው። ለዚህም የዛጉዌ አገዛዝን የአገዎች፣ በሸዋ ምስራቅ ዳርቻ የኢፋት ሱልጣናዊ አሰተዳደርን በዋነኛ ምስሌነት መጥቀስ ይቻላል። በዚህ ጉዳይ ሪቻርድ ፓንክረስት The Ethiopian Borderlands በሚለው መፅሀፍ “እንደ አል ኡማሪ አገላለፅ ኢፋት ከኢትዮጵያ የእስልምና ተከታይ ጠ/ግዛቶች ትልቁ፣ ሀብታምና ኗሪዎቹም ሀበሽኛ ተናጋሪዎች ነበሩ ያለው ምናልባት አማርኛ ተናጋሪዎች መሆናቸውን ለመግለፅ አስቦ ያለው ነበር” በሚል አቀራረብ አስቀምጠውታል። ዛሬ በሸዋ ይፋቴዎች በአመዛኙ ክርሰትያኖች ቢሆኑም አነስ ቢሉም እስላሞችም አሉባቸው። ባህላቸውና ቋንቋቸው አል ኡማሪና ፓንክረሰት እንዳስቀመጡት አማርኛ ነበር፤ አሁንም ነው። 

አገዎች ግን በበኩላቸው ጥንታዊና የቅድሚያ መሰረታዊ አሰፋፈር በመላው ሰሜናዊ ኢትዮጵያ ያላቸውና በራሳቸው ቋንቋ ለብዙ ሺህ ዓመቶች በመጠቀም የኖሩ የበርካታ ታሪክ ባለቤቶች ናቸው። የአማራው ዝርያ ምንጭና አማራም የበህር ልጃቸው ለመሆኑ ጥርጥር የለውም። International Encyclopedia of Linguistics ላይ ዊሊያም ፍራውሊ እንደፃፉት “ያለምንም ጥርጥር (certainly) በጥቁር አባይ በስተሰሜንና በቤሽሎ ተፋሰስ አቅራቢያ በዛሬዎቹ በጌምድርና ወሎ አማራ የሚባል ጥንታዊ ግዛት ነበር …” ብለው ቋንቋን መሰረት ያደረገና ሌሎች ታሪካዊ ሀቆችን ተንትነው አስፍረዋል።

 ሮላንድ ኦሊቨር ከፍ ሲል የተጠቀሰውን አጠናክሮ በሚከተለው አባባል ገልፆታል “በአማራ ድሮ ክርስትያኖች በ9ኛው ክ/ዘ ሲሰፍሩ በዘገቡት ማስረጃ አማራ ተብሎ የሚጠራ ከነርሱ የተለየ ጎሳና ቋንቋ የሚናገር ህዝብ በተከዜ ወንዝና በምስራቃዊ ሸለቆ ባሉት የአባይ ገባሮች መካከል ስለመኖሩና ይህም ተተኪ የሌለውና ጠቃሚ መረጃ (invaluable note) በአቡነ ተ/ሀይማኖት ገድልና ማስታወሻ ተጠብቆ እንደሚገኝና መረጃውም የአቡኑ የቅም ቅም አያቶች ከ18 ትውልድ በፊት ዳውንት በሚባል የአማራ አገር መስፈራቸውን ያመለክታል።” ይሄው የታሪክ ተመራማሪ አማራዎች በ9ኛው ክ/ዘ ከክርስትና ጋር መተዋወቅ ቢጀምሩም ለበርካታ ዘመናት በተለያዩ ነገሮች አማኒዎች (አማኞች) እንደነበሩ በሰፊው ዘግቧል። 

በአማራ የመጀመሪያው ገዳም የተመሰረተው በድሮው አንጎት (የዛሬው ወሎ) ሐይቅ ከ12 ክ/ዘ ወይም አንድ ሺህ አንድ መቶ ዓመት በፊት ከአክሱም ተሰደው በመጡ ሰዎች እንደሆነ ይነገራል። ከፍ ሲል የተጠቀሰው ተመራማሪ አያይዞም “በአንጎት የሐይቅ ደሴ ገዳም የምስረታ ታሪክ በዘጠነኛው ክ/ዘ እንደሆነና ባቅራቢያው የሚገኘው ቤተክርስትያን (ተ/ሀይማኖት) ከተሰራ 720 ዓመት በኋላ በሙስሊም ጦር (ግራኝ ወረራ) እ.አ.አ በ1532 መቃጠሉን የታሪክ ዘጋቢ ለነበረው አህመድ ኢብራሂም ተነግሮት ነበር” በሚል ሁኔታውን ለማብራራት ተጠቅሟል። (በዚህ ጥቅስ በቅንፍ የተቀመጡት በራሴ ለመረዳት እንዲያመች አካትቻለሁ)። 

ሆኖም በላስታ ያለውንና አስደናቂውን የአቡነ መርቆሪዮስ ውቅር ድንጋይ ገዳም ስንመላከት ከ አንድ ሺህ አራት መቶ ዓመት በፊት በአክሱሞች ዘመን መሰራቱ (ከዛጉዌ መግነን አስቀድሞ) ምናልባትም አማራ ውሰጥ ክርስትና የሮላንድ ኦሊቨርና ሌሎችም ጥናቶች ከሚሉት 300 ዓመት ቀድሞ ገብቷል ማለትም ይቻል ይሆናል የሚል አቀራረብም አለ። ዛሬ በሐይቅ የእስጢፋኖስን ገዳም ለሚጎበኝ በጥንት አማራው በዘንዶ አማኒ (አማኝ) እንደነበር አመላካች የሆኑና ለሚመለክለት ዘንዶ መስዋዕት ማቅረቢያ የአርኪዮሎጂ ቅሪት ቁሳ ቁሶች በክብር ተጠብቀው ስለሚገኙ መመልከት ይቻላል። በዚህ ነጥብ መካተት ያለበት ደግሞ ዳሞትና ጋፋት ከአማራ ጋር የነበራቸው የግዛት፣ የባህልና የቋንቋ ትስስር ነው። ባአሁኑ ወቅት ከአባይ ሸለቆ በስተደቡብ የሚገኘው ከኦሮሞ ወረራ በኋላ ወለጋ በተባለው ሰሜናዊና ሰሜን ምዕራባዊ መሬቶች ጥንታዊ የዳሞት ሕዝብ ሰፍሮ የኖረባቸውና ያስተዳደራቸው ናቸው። 

በአቡነ ተ/ሀይማኖት ገድል ተፅፎ የሚገኘው ማስረጃ ደግሞ የዳሞት ድንበር እስከ ጀማ(ጃማ) ወንዝ የዘለቀና ዛሬ ምዕራብ ሸዋና ሰሜን ሸዋ ተብለው በኦሮሞ ውስጥ እንዲከካተቱ የተደረጉትን ግዛቶች የሚያጠቃልል እንደሆነ በአስረጅነት ሰፍሯል። ዳሞት በዘር ግንድ፣ በባህል፣ ልምድና ሀይማኖት የአገውና የአማራ ደም ያላቸውና ቋንቋቸውም የአገውና አማርኛ ቅይጥ ወይም በክርስትና ከአክሱም ወደ ታች መስፋት በተነሳ ግዕዝ ተናጋሪዎች እንደሆኑ ታሪክ ይጠቁማል። ጋፋት በመሰረቱ አማራ ሲሆን ቋንቋው ራሱ አማርኛ ሆኖ በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ (ክሪዮል) ወይም የወፍ ቋንቋ አጥብቀው በልምድ ሲወርድ ሲዋረድ ይጠቀሙ እንደነበር በጥናት ተረጋግጧል። 

እዚህ ላይ ጋፋት ሞቷል የሚባለው የወፍ አፍን መሰረት ያደረገ የነበረው መግባቢያዊ ስልትና ልማድ መጥፋቱን የተንተራሰ እንጂ የሕዝቡን ታሪካዊ የዘር ግንድና ባህል በተጨማሪም የቋንቋውን ይዘት፣ ቅርፅና መገለጫ 99 በመቶ አማርኛ መሆኑን ያላገናዘበ ድምዳሜ እንደሆነ ተመራማሪዎች ደርሰውበታል። ዎልፍ ሌስላው የትባሉት የቋንቋ ተመራማር የጋፋት ሰነዶች በሚለው 50 ዓመት በፈጀ ጥናታቸው እንዳጠቃለሉት “የቋንቋ ጥናት አዋቂን ሊስበውና እንድያውቀው የምሻው በምርምሬ በጋፋት ነጋዴዎች፣ ቀልደኞች (አዝናኚዎች)ና ውቃቢ ያለባቸው ሁሉ አማርኛ ተናጋሪዎች ሲሆኑ ለስራቸው መጠቀሚያ (professional purposes) ቢበዛም ቢያንስም አርቲፊሻል ቋንቋ ይጠቀሙ እንደነበር ነው።” በዚህ ነጥብ ላይ በአማርኛና ጋፋት መካከል ልዩነት አለመኖሩን ማወቅ ካስፈለገ (Gafat Swadesh List the Rosetta Project) መመልከት በቂ ይመስለኛል። 

ይህ ሰነድ ቃል በቃል ጋፈትና አማርኛ አንድ መሆናቸውን በማያሻማ መልኩ አጠናቅሮ አቅርቦታል። የጋፋትን ግዛት በተመለከተ ሮናልድ ኦሊቨር የሚከተለውን ፅፏል “…ሁሉም ጥንታዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ጋፋት የሚገኘው በዋነኛው አዋሽ ወንዝ ጅረትና (headwaters) በአባይ ወንዝ ሸለቆ መካከል ነው። … አንዳንድ የጋፋት ጎሳዎች ከታችኛው የጀማ (ጃማ) ወንዝ አካባቢ እስከ ሙገር ወንዝ … የግማሽ ጨረቃ ቅርጽ ያለውን ሰፊ መሬት … ወደ ምዕራብ በመካከለኛው ዘመን ዳሞት እስከ ጉደር ወንዝ ይደርሳል።” ይህን ሁሉ መዘርዘር አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት የአማራ ሕዝብ በውስጡ በርካታ ጎሳዎች እንደማንኛውም ብሔረሰብ አካቶ የያዘና አንድ ወጥ አለመሆኑን ለማመልከት አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘሁትና ማንም በዚህ ነጥብ ሲወያይ ባለመስማቴም ጭምር ነው። 

ለምሳሌ በታሪክ ደምቢያ፣ ወገራ አንጎት(ያሁኑ ወሎ) ፣ ጎጃም፣ መንዝ፣ ተጉለት፣ ቡልጋ በራሳቸው የሚተዳደሩ አማራዎች እንደነበሩ ከብዙ በጥቂቱ መጥቀስ ይቻላል። በተጨማሪም የአማራውን ታሪካዊ የግዛት ስፋትና አሰፋፈር በማያሻማ ሁኔታም ማስቀመጡ ካለንበት ተጨባጭ እይታ አኳያ አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘሁት ነው። አማራ ከአረብ አገር ፈለሰ የሚባለው ደግሞ ስለትክክለኛነቱ አሳማኝ ታሪካዊ ማስረጃ ያልተገኘበትና በጥናት ላይ ያልተመረኮዘ አገላለጥ ለመሆኑ ጠንካራ ጠቋሚዎች አሉ። ይህንን ፅሁፍ አማራ ኩሽ ነው ብዬ ነበር የጀመርኩት። እንደሚታወቀው ሁሉም የአረብ ታሪክ ፀሀፊዎች ማለት ይቻላል እንደ ጥንት ግሪኮች ኢትዮጵያን የኩሽ አገር ብለው እንደሚጠሯት ማንም ያውቃል። ለዚህም ዲዮደረስ ሲኩለስን (90-21ክ/ል/በ)፣ ሄሮዶተስ(490- 425 ክ/ል/በ) ወዘተ. መጥቀሱ በቂ ነው። እዚህ ላይ ግልፅ መሆን ያለበት ኢትዮጵያ የሚለው መጠሪያ ሰፊ ግዛትን ከደቡብ ግብፅ ጀምሮ እስከ መላው የአፍሪካ ቀንድ በድሮ ግዜ ይሸፍን እንደነበር መታወቅ አለበት። 

Myth, Hypotheses and Facts በሚለው ታሪካዊ ትንተና “የኩሽ ሕዝቦች በጥንት ግዜ በመላው አረቢያ፣ ደቡብ ሜሶፖታሚያ፣ ኤላምና እስከ ሕንድ ድረስ ይኖሩ ነበር” ይላል። በዚሁ ፅሁፍ “ደቡብ አረቦች በመጀመሪያ (originally) ኩሾች(ኢትዮፒክ) ነበሩ። ጥንታዊ ሳባዊያን ከኑቢያኖችና ሀበሾች ጋር የቅርብ ዝምድና (closely related) ነበሩ” ይላል። አማርኛ መሰረቱ ግዕዝ በመሆኑና ፊደሉ ደግሞ አሲራዊያን አረቦችን ወደ ሴምነት ከለዋጧቸው በኋላ በተፈጠረው ቋንቋ ጋር ስለሚወራረስ በተጨማሪም አክሱማዊያን ስልጣኔያቸውና በደምም ወዘተ. ከመካከለኛው ምስራቅ (አረቢያን) ጨምሮ ስለሚዛመድ፣ አማራው ደግሞ በጉርብትና ካለው ኩታ ገጠምነት የተነሳ በባህልና ሀይማኖት ተከታይ ሆኖ ስለተገኘ (አማራውን) ሴማዊና መጤ ነው የሚለው አገላለፅ መሰረት የለውም። 

 ለምሳሌ አገዎች ቀሚርንና ሌሎቹን ጨምሮ ልክ እንደ አማራው በአክሱሞች ባህልና ሀይማኖት ተከታይ ቢሆኑም ቋንቋቸው ኩሽ ስለሆነ ከሴም ጋር በተያያዘ ስማቸው ሲጠራ አይሰማም። ኮድካ ሶማሊንግ አልቢድል Ethnic groups of Ethiopia ብሎ ባቀረበው ፅሁፍ “አማራ ልክ እንደ አፋር ኩሽ ሲሆን አማርኛ ቋንቋው ግን … ከሴም ቋንቋዎች ጋር ይመደባል … ለፅሁፍ የሚጠቀምበት ፊደሉም ከ2ሺህ ዓመት በላይ ያስቆጠረና በጥንታዊ አረብ አፃፃፍ ላይ የተመሰረተ ነው” ሲል አብራርቷል። ባጭሩ እንግሊዝኛ ተናጋሪዎች የሆኑ አፍሪካዊያን፣ አረብኛ የሚናገሩ ሰሜን አፍሪካዊያን፣ ስፓኒሽ ተናጋሪ ደቡብ አሜሪካኖች፣ ፈረንሳይኛ የሚጠቀሙ አፍሪካዊያንና የሩስያን ቋንቋ የሚናገሩ የድሮው ሰቭየት አካል የነበሩ ሁሉ ወዘተ. እንግሊዞች፣ አረቦች፣ ስፓኞች፣ ፈረንሳዮች ሩስያዎች ወዘተ… እንዳልሆኑ ስለሚታወቅ አማራን ከአክሱሞችና ተወላጆቻቸው በማያያዝ ሴምና አረባዊ ማድረጉ ትክክል አይደለም። 

በ7ኛው ክ/ዘ አካባቢ የአክሱም ሀይልና ሀብት በአረቦች በቀይ ባህር፣ ኤደን የባህረ ሰላጤ፣ በመካከለኛው ምስራቅና ግብፅ ወዘተ… ድልን በድል መቀዳጀትና ሀያል መሆን አክሱም በከፋ ሁኔታ እንዲዳከም ተገዷል። Kingdom of Africa Cradle of Civilization and Humanity በሚባለው መፅሀፍ “በአክሱም መዳከም ተጠቅመው የቤጃ ሰዎች ወደ (አክሱም) ሲዘምቱ አክሱሞች በበኩላቸው ወደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች የነበሩ በትናንሽ ግብርና ተዳዳሪዎችን በማሸነፍ በአማራ ሰፍረዋል።” ይህ በግልፅ የሚያመለክተው ልክ እንደ አቡነ ተክለሀይማኖት ገድል አማራ ከአክሱሞች የተለየና ከየመን ወይም አረብ አገር ፈልሶ ያልመጣ መሆኑን ነው።

በአጠቃላይ በተለያዩ ግዜዎች ገነው የነበሩት አክሱሞች ዛግዌ፣ አዳል (ሀውዳል) በተለይም በግራኝ ዘመን፣ የኦሮሞ ወረራ ወዘተ. በአማራው ላይ አዎነታዊና አሉታዊ ተፅኖዎች አሳድረዋል። ለምሳሌ ከክርሰትና ሀይማኖት ጋር በተያያዘ የተከተለው መተዋወቅና የአማርኛ ቋንቋ መጎልበት እንዲሁም በንግድ ልውውጥ መጠቀምና አቅምን ማጠናከር ለአማራው የጠቀሙ ክስተቶች ሲሆኑ በተለይም ከግራኝ በኋላም በኦሮሞ ወረራ የብዙ መቶ ሺህና ከዛም በላይ አማራዎች መጨፍጨፍ፣ የገዳሞችና ታሪካዊ ንብረቶች መውደምና የቅርሰ መሬት(ታሪካዊ ግዛት) በሀይል መነጠቅና የመሳሰሉት አፍራሽ ተፅኖዎች ናቸው።

 ከፍ ሲል በተጠቀሱት ጉዳዮችና ሌሎችም ንክኪዎች ሳቢያ አማራው ከተለያዩ ህዝቦች፣ ባህልና ልምዶች ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ እንዲተዋወቅና እንዲዋለድ አስገድዶታል። ስለዚህ James Minahan, Minatu e Empires … በሚላው ፅሁፍ “የዛሬው አማራ የሴም፣ የሀምና የጥቁር አፍሪካ ድብልቅ የመደብ ጀርባ ያለው ነው።” ሲል ሀቁን አቅርቧል። በአማራው ላይ ወረራና የግዛት መስፋፋትን ተገኑ ስላደረገው ኦሮሞ Richard Pankhurst በዚህ ፅሁፍ በጠቀስኩት መፀሀፋቸው እንደሚከተለው አቅርበውታል “እ.አ.አ ከ1562-1570 በሉባ ሀርሙፋ አማካኝነት ወደ አማራ እስከ በጌምድርና አንጎት ዘልቀዋል። … እ.አ.አ. 1570-1578 በሮበሌ የሉባ መሪነት ኦሮሞ ተዋጊዎች ሸዋን አውድመው ጎጃም ድረስ ገብተዋል። በወቅቱ የኦሮሞ መስፋፋት በአፄ ስርፀ ድንግል ዝዋይ ላይ የጋላ ጦርን ጠንክረው ተዋግተው ወደ ደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ አባረዋቸው ነበር።

ነገር ግን እ.አ.አ ከ1586 – 1594 የኦሮሞ ግፊትና መስፋፋት በሙለታ የሉባ መሪነት ቀጥሎ አብዛኛው ሸዋና ዳሞት በቁጥጥራቸው ስር ውለዋል።” በዚህ ፅሁፍ በርካታና ግልፅ ታሪካዊ ክስተቶችን በማቅረብ የመንደርደሪያ ማስረጃዎችን በማመላከት ለደጋፊና ተፃራሪ ፀሀፊዎች ወደፊት መወያያ እንዲሆን ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ተሞክሯል። በአማራው ላይ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ የተጀመረው የኦሮሞ ወረራ፣ መስፋፋትና ጭፍጨፋ አሁንም በኦነግ አማካኝነት ቀጥሎ በመካሄድ ላይ መሆኑን በዝርዝርና በማስረጃ አስደግፌ በሌላ ፅሁፍ እመለስበታለሁ።

(ጸሃፊውን በዚህ ኢሜል ማግኘት ይቻላል Telaashenafee74@yahoo.com)

Ethiopian Orthodox Church Holy Synod: Open Letter to United Nation Concerning Waldeba Monastery


Ethiopian Orthodox Church Holy Synod CrossTo: Ban Ki-Moon

United Nations Secretary General
760 United Nations Plaza
New York, 10017, USA

Open letter concerning “Waldeba Monastery in Ethiopia”

Yor Excellency,
We, members of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church Holy Synod in Exile, and followers of the Ethiopian Orthodox faith who live in the Diaspora, are gravely concerned about the dire threat posed against Waldeba Monastery in Ethiopia. This prestigious monastery, found in the fifth century, is one of the oldest in Christendom. Instead of enjoying a status deserving to a sacred site or to a pride jewel of the nation, it is being subjected to the chaos that entailed large scale construction and farming projects recently launched by the approval of the Government of Ethiopia. To make way for the road and to clear land for the sugar factory, irrigation dam, sugarcane plantation, burial grounds have been and are being desecrated. Residents are being uprooted without consent from the land their ancestors occupied for generations

.We are certain it is known to you that the government of Ethiopia has been and is leasing sizeable tracts of land to foreign companies and to Ethiopians who support its oppressive regime. These large farms are intended to grow crops for the purpose of exporting food while hundreds of thousands of Ethiopians suffer from lack of food every year. Ethiopians in the Diaspora have expressed their protest against this cheme that forcefully dislodges poor Ethiopian peasants from their homeland. We, in general, are not against development projects that benefit the people of Ethiopia and that do not disrupt the peace and harmony that exists among its peoples.

The Ethiopian Orthodox Church, rich in tradition, is one of the first churches that embraced monastic life. The monasteries were not only spiritual communities that offered a life of prayer, but they were also sources of literature, arts, music, and culture. As a result, the Ethiopian Orthodox Church is credited for providing and preserving the alphabet, calendar, music, and many other elements of everyday life that are unique to Ethiopia.

The Waldeba Monastery, founded around year 490, located in one of the remote regions in the country and is regarded among the Holiest places in the Ethiopian Orthodox Church. It has been a place that produced many of the Church scholars and it is still actively accepting aspiring priests and monks. Like many monasteries, it is also a refuge to those fleeing imminent danger. It is a customary for members of the monastic communities of Waldeba, pray for world peace, and for the well being of all human kind.

With the exception of three brief disruptions, caused by internal and foreign invaders, the peaceful monastic life (living, working, praying and learning together) has been treasured by all rulers in the past and governments in recent history of Ethiopia. Government decree in the 15th century officially expanded the land of the monastery and marked its boundary to be within the four rivers and streams that surround the monastery. In subsequent year, the sovereignty of the monastery was farther asserted to protect the monastery from possible invaders and settlers. Since then, governments throughout history, including the communist Derg, honored the sovereignty of the monastery and in no way interfered in its affairs.

Given its record, Ethiopians are not surprised such an honored tradition is disregarded by their current government. This place of contemplation and prayer deserves additional protection and attention from international organizations and individuals who understand the negative impact of industrialization brings to protected regions. The peace and tranquility of this prestigious monastery and surrounding area could forever be altered by the infrastructure being built to accommodate the number of people that will be brought in to work directly or indirectly with the farm, the factory, and the dam.

Monks from the communities of the Monastery have been trying in vain to express their concerns to government authorities. Prior to the start of the projects, hearings were not held and leaders from the monastic communities were never consulted. After the news broke recently, as a public relation effort, mock meeting were held in which the government officials dominated the discussions and overwhelmed the soft-spoken monks who are familiar with silence not debate or argument. Those who are raising their voices against the impact of the project are being targeted and systematically silenced.

Many monks and residents of the region have protested the project, but the media (only government-controlled ones exist in Ethiopia), declare as if the Monastic community has support the project and that the Waldeba Monastery is not affected by the project activity. This is far from the truth and the people of Ethiopia recognize that their oppressive government cannot be trusted to come forth honestly. Church leaders in Ethiopia seems unable/unwilling to express their apprehension or to support the monastic communities of Waldeba be given proper forum to voice their concerns.

Followers of the Ethiopian Orthodox Church are tracking the recent developments closely and are praying that Almighty God bring and end to the chaos. Ethiopians are God-fearing people and will not resort to any violent actions in order to assert their rights or protect the integrity of their church. However, if demands to assure the preservation of Waldeba Monastery are not considered, it is anyone’s guess to what level distressed people could resort. At the moment, the people of Ethiopia are attempting to involve international organizations and civic groups to promote their cause. That is why The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church Holy Synod in Exile is appealing to your office on behalf of the people of Ethiopia so your office may influence the government of Ethiopia.

We call on the Ethiopian government to:
  1. Freeze any activity that will directly impact the Waldeba Monastery and people in the region.
  2. Conduct environmental, social and cultural impacts of the project to the monastery.
  3. Respect freedom of religion and worship: that includes restraining from violating properties of the Church, its religious learning centers and its sacred sites of the Ethiopian Orthodox Church.
  4. Engage in direct dialog with the representatives of the monastic communities of Waldeba to resolve current issues and avoid further instigations.
  5. Place value on historical, cultural and intellectual contributions of Waldeba Monastery to the people of Ethiopia and preserve its prestige for the generations to come.
We hope that the United Nations, along with the rest of the international community, do not miss an opportunity to stand by the people of Ethiopia in their effort to preserve Waldeba Monastery, one of its oldest treasures, from eventual destruction.
May God be with us all.
Aba Melketsedek Workneh
Archbishop of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church and General Secretary of the Holy Synod in Exile.

Wednesday, April 18, 2012

UN special rapporteur on human rights for migrants are concerned about the return agreement with Ethiopia

    Dated:  March 23, 2012  
                                            UN Special Rapporteur on the human rights of migrants
                                                                                   Francois Crepeau,  (OHCHR)
To His Excellency
Mr. Steffen Kongstad
Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary
Permanent Representative of Norway
Permanent Mission of Norway to the United Nations Office at Geneva
NATIONS UNIES
HAUT COMMISSARIAT DES NATIONS UNIES AUX DROITS DE L’HOMME
PROCEDURES SPECIALES DU CONSEIL DES DROITS DE L’HOMME    UNITED NATIONS
OFFICE OF THE UNITED NATIONS HIGH COMMISSIONER FOR HUMAN RIGHTS
SPECIAL PROCEDURES OF THE HUMAN RIGHTS COUNCIL
Mandate ,of the Special Rapporteur on the human rights of migrants.
Téléfax: (41-22)917 9006
Télégrammes: UNATIONS, GENEVE
Téléx: 41 29 42
Téléphone: (41-22) 917 9359
Internet www.ohchr.org
E-mail: urgent-action@ohchr.org
REFERENCE: AL, G/SO 214 (106-10)
NOR 1/2012
Address; Palais des Nations CH-1211 GENEVE 10
Excellency.
His Excellency
Mr. Steffen Kongstad
Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary
Permanent Representative of Norway
to the United Nations Office at Geneva
Avenue de Budé 35 bis
Case postale 274
1211 Geneva 19

I have the honour to address you in my capacity as Special Rapporteur on the’ human rights of migrants pursuant to General Assembly resolution 60/251 and to Human Rights Council resolution 17/12. In this connection, I would like to bring to the attention of your Excellency’s Government information I have received regarding the repatriation agreement between Norway and Ethiopia. I will also be sending a similar letter to the Government of Ethiopia.

According to the information received: A Memorandum of Understanding (MOU) between the governments of Norway and Ethiopia concerning assisted return of Ethiopian nationals residing in Norway was signed on 26 January 2012. Ethiopian nationals whose request for a refugee status or residence permit has been rejected, and those with pending application for asylum who decide of their own free will to return to Ethiopia are being offered’ an opportunity to return voluntarily to Ethiopia with support from the , Norwegian authorities.

The MOU provides that Norwegian authorities commit themselves to sharing with the Ethiopian authorities “as much information as possible with regard to the returnees” (article 3.4). It is alleged that this could put them at risk when they are returned to Ethiopia. Furthermore, the MOU does not provide for guarantees that the returnees will not be subjected to harassment, threats, persecution, discrimination or criminal investigations upon their return to Ethiopia. The MOU (annex 2) provides that the Norwegian authorities shall submit a return application (for the persons to be returned) to the Ethiopian Ministry of Foreign Affairs and to the National Intelligence and Security Services/Immigration.

The MOU (annex 1) further provides that the Ethiopian Administration for Refugee and Returnee Affairs (ARRA) will be responsible for the implementation of the return and reintegration programme in Ethiopia. It is alleged that ARRA does not have any experience relating to reintegration of individuals. According to the MOU, ARRA will receive a sum of money per returned person (NOK 26 000 per person plus administrative costs).

-Reportedly, repatriation agreements Norway has entered into with other countries in the past have provided that personal information concerning the content of asylum application should not be disclosed, and that the receiving country undertakes to protect the returnees against harassment, threats, persecution, discrimination and criminal prosecution. Furthermore, in the past, reintegration programmes have been managed by IOM or UNHCR.

Allegedly those who do not return voluntarily will be returned by force, starting on 15 March 2012. This may affect up to 400 persons, many of whom have been living in Norway for many years, established families in Norway and worked there legally until January 2011, when their work permits were withdrawn. Reportedly, persons who do not return voluntarily and who are returned by force will not receive reintegration support.

It is alleged that the freedoms of opinion and expression and peaceful assembly and association are not guaranteed in Ethiopia. Many of the rejected asylum seekers residing in Norway claim to have been political activists in Ethiopia, and fear that their lives could be in danger if they are returned to Ethiopia. It is further alleged that the deportations may result in rights abuses such as torture or ill-treatment.

Children who were born and raised in Norway, and who have never even been to Ethiopia will reportedly also be subjected to forced return. Reportedly, primary education is not free or compulsory in Ethiopia, which could lead to a regression in these children’s enjoyment of their right to education. Furthermore, 46 children who are either Norwegian citizens or have a permanent residence in Norway and who will remain there, will be separated from either their mother or father, whose asylum application has been rejected, and who will be subjected to forced return.

Concern is expressed at the lack of safeguards in place for the return and reintegration process- Concern is also expressed for the physical and mental integrity of persons who have been politically active with the Ethiopian opposition, should they be forcibly returned to Ethiopia. Concern isfurther expressed that forced return may not be in the best interests of the children concerned.

While I do not wish to prejudge the accuracy of these allegations, I would like to remind your Excellency’s Government that the enjoyment of the rights guaranteed in the International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR), ratified by Norway on 13 September 1972, is not limited to citizens of States parties but “must also be available to all individuals, regardless of nationality or statelessness, such as asylum seekers, refugees, migrant workers and other persons, who may find themselves in the territory or subject to the jurisdiction of the State Party” (CCPR/C/21/Rev.l/Add. 13 (2004), para. 10).

Furthermore, I would like to stress that your Excellency’s Government has the obligation to protect the right to physical and mental integrity of all persons within its territory or subject to its jurisdiction. Article 7 of the ICCPR provides that “No one shall be subjected to torture or to cruel, inhuman or degrading treatment or punishment. I would also like to recall article 3 of the Convention Against Torture and other Cruel, Inhuman or Degrading Treatment or Punishment, ratified by Norway on 9 July 1986, according to which no State Party shall expel, return (“refouler”) or extradite a person to another State where there are substantial grounds for believing that he would be in danger of being subjected to torture.

 For the purpose of determining whether there are such grounds, the competent authorities shall take into account all relevant considerations including, where applicable, the existence in the State concerned of a consistent pattern of gross, flagrant or mass violations of human rights. In this respect, I would like to refer to the Committee against Torture, which in 2010 was “deeply concerned about numerous, ongoing and consistent allegations concerning the routine use of torture by the police, prison officers and other members of the security forces, as well as the military, in particular against political dissidents and opposition party members, [...]” in Ethiopia (CAT/C/ETH/CO/1, para 10.

I would also like to draw your attention to article 33 of the 1951 Convention on the Status of Refugees and its protocol, ratified by Norway on 23 March 1953 and 28 November 1967 respectively, which stipulate that no Contracting State shall expel or return (“refouler”) a refugee in any manner whatsoever to the frontiers of territories where his life or freedom would be threatened on. account of his race, religion, nationality, membership of a particular social group or political opinion.

While noting that your Excellency’s Government is currently working on a white paper on asylum-seeking children (Stortingsmelding om barn på flukt), it is of particular concern that the MOU does not seem to take into account the particular protection measures that should be put in place for children. In this regard, allow me to remind your Excellency’s Government of article 3 of the Convention on the Rights of the Child, ratified by Norway on 8 January 1991, which provides that in all actions concerning children, whether undertaken by public or private social welfare institutions, courts of law, administrative authorities or legislative bodies, the best interests of the child shall be a primary consideration. In this respect I would like to refer to the concern expressed by the Committee on the Rights of the Child in 2010, that in Norway, “the principle of primary consideration of the best interests of the child is not yet applied in all areas affecting children, such as [...] immigration cases” (CRC/C/NOR/CO/4, para 22).

 I would also like to recall article 2(2) of the Convention which provides that all appropriate measures shall be taken “to ensure that the child is protected against all forms of discrimination or punishment on the basis of the status, activities, expressed opinions, or beliefs of the child’s parents, legal guardians, or family members”.
In the event that your investigations -support or suggest the above allegations to be correct, I urge your Excellency’s Government to take all necessary measures to guarantee that the rights and freedoms of Ethiopian nationals at risk of forced return are respected.

As it is my responsibility, according to the mandate entrusted to me by the Human Rights Council, to clarify all information brought to my attention, I would greatly appreciate additional details from your Excellency’s Government concerning the above MOU and its implementation plan. I would in particular appreciate to receive information on the following points:

1.    Are the facts alleged in the above summary of the case accurate?
2.    How will your Excellency’s Government monitor how ARRA spends the money it receives for the implementation of the return and reintegration programme?
3.    What is the role of the National Intelligence and Security Services in the return and reintegration process?
4.    How will your Excellency’s Government ensure that the authorities in Ethiopia comply with the absolute prohibition of torture vis-a-vis the returnees?
5.    What measures has your Excellency’s Government taken or does it intend to take to ensure an individual assessment of all Ethiopian nationals subjected to forced return; those who may be in need of international refugee protection or who are in need of human rights protection for other reasons?
6.    What measures has your Excellency’s Government taken or does it intend to take to ensure an evaluation of the best interests of the child in relation to each Ethiopian child (any person under the age of 18 years) who may be subjected to forced return?

7.    Please provide information on the status of the negotiations relating to other repatriation agreements between your Excellency’s Government and other countries, please indicate the contents of these agreements, and please send me a copy of the draft texts of the agreements, if available.

I would greatly appreciate receiving the above information from your Excellency’s Government within 60 days. Your Excellency’s Government’s response will be made available in a report to the Human Rights Council.
I remain at your disposal for any further clarification you may require and hope to . be able to continue this constructive dialogue with you and your Excellency’s Government. Please note that I can be contacted through the Office of the High Commissioner for Human Rights (Ms. Christel Mobech at cmobech@ohchr.org, and Ms. Federica Donati at fdonati@ohchr.org, tel: + 41 22 917 9995 / + 41 22 917 9496; or any of them at: migrant@ohchr.org).
Please accept, Excellency, the assurances of my highest consideration.
Francois Crepeau
Special Rapporteur on the human rights of migrants

Look the original letter here: http://tolvtejanuar.org/2012/04/18/fns-spesialrapportor-pa-menneskeretter-for-migranter-er-bekymret-over-returavtalen-med-etiopia/