Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Saturday, December 8, 2012

ቅዱስ ሲኖዶሱ ‘አቡነ መርቆርዮስ ቀደም ሲል በተወሰነላቸው መሠረት መመለስ ይችላሉ’ አለ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን አባቶች፣ በሰሜን አሜሪካው የሰላምና አንድነት ኰሚቴ አስተናጋጅነት፣ ፫ኛውን እርቀ-ድርድር ባለፈው ረቡዕ ዳላስ፣ ቴክሳስ ውስጥ መጀመራቸው፤ ለዚሁ ውይይት፣ ያዲሳባው ቅዱስ ሲኖዶስ ፬ ልዑካን፣ የስደተኛው ቅዱስ ሲኖዶስ ፬ ልዑካን እየተሳተፉ መሆናቸው ይታወቃል። ምን ላይ ናቸው? እስካሁን የሰማንው ነገር የለም፣ ደውለን ለማግኘት ያደረግንው ጥረትም አልተሳካም።


ብፁዕ አቡነ ናትናዔል
ይህ በእንዲህ እንዳለ ባለፈው ማክሰኞ ለብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ፣ ከኢትዮጵያው ፕሬዚደንት ግርማ ወልደ-ጊዮርጊስ የተጻፈ «ከሙሉ ክብርዎና ሥልጣንዎ ወደ አገርዎ ገብተው መንበርዎ ላይ እንዲሆኑ» የሚል፣ ፊርማቸውና ቲተራቸው ያረፈበትን፣ በኋላም እራሳቸው ያረጋገጡትን ደብዳቤ፣ በኋላ ደግሞ በራሳቸው አንደበት ተሰርዞ «በማያገባኝ ነበር የገባሁት» ያሉበትን ማሰማታችንና ማስተላለፋችን ይታወሳል።

 ቅዱስ ሲኖዶሱ ‘አቡነ መርቆርዮስ ቀደም ሲል በተወሰነላቸው መሠረት መመለስ ይችላሉ’ አለ::


No comments:

Post a Comment