Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Tuesday, July 17, 2012

በዳባት ከተማ አንድ ነዋሪ የቀበሌውን ባለስልጣን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ሰዎችን ገደለ

ሐምሌ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

በሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ወረዳ ቀበሌ 03 ነዋሪ የነበረ አንድ ግለሰብ የቀበሌው ሊቀመንበር የሚያደርስበትን ጫና ለመቋቋም ባለመቻሉ ሊቀመንበሩን፣ ባለቤቱን እና ሌላ አንድ የሊቀመንበሩ አጋር የሆነ ሰው ገድሎ ሌላ አንድ ሰው ደግሞ ክፉኛ አቁስሎአል።

በፍትህ እጦት የተማረረው ግለሰብ ግድያውን ከፈጸመ በሁዋላ እጁን ለመንግስት የሰጠ ሲሆን፣ ከዚህ በሁዋላ እንደፈለጋችሁ አድርጉኝ የልቤን አድርሻለሁ በማለት መናገሩን ዘጋቢዎቻችን ገልጠዋል።

ግለሰቡ ከሊቀመንበሩ ጋር ያለውን ውዝግብ በድርድር ለመፍታት ጥረት ያደርግ ነበር ተብሎአል።

 Source: ኢሳት ዜና:-

No comments:

Post a Comment