Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Wednesday, November 21, 2012

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለሁለተኛ ጊዜ ተዘረፈ

ኢሳት ዜና:- በአሁኑ ዝርፊያ ከ 50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት አጥቷል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የአይቲኤስሲ ላብራቶሪ ሰሞኑን ለሁለተኛ ጊዜ ተዘረፈ፡፡

ሪፖርተር ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ለሁለተኛ ጊዜ ሰሞኑን የተዘረፈው የ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢንስቲትዩቱ ላብራቶሪ እጅግ በጣም ውድ የሆኑ፣ የዘመኑን ቴክኖሎጂዎች ያካተቱና በብዙ ሚሊዮን ብር የሚገመቱ ንብረቶቹን አጥቷል።


ዝርፊያው የተፈፀመው የዲፓርትመንቱን በር ቁልፍ በመስበር እንደሆነም ምንጮቹ ገልጸዋል። የተወሰዱት ኮምፒውተሮችና የላብራቶሪ ዕቃዎች ግምት ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ሊበልጥ እንደሚችል ያመለከተው ጋዜጣው፤ጉዳዩን ፖሊስ ይዞ እየመረመረው መሆኑንም ጠቁሟል፡፡

በዝርፊያው ተጠርጥረው ከታሰሩት ውስጥ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በፍሪላንሰርነትና በቋሚነት የሚያገለግሉ ሠራተኞች እንደሚገኙበት ተመልክቷል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ተከስቷል ስለተባለው ዝርፊያ ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጠየቁት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ነፃነት ይልማ፦ ‹‹ጉዳዩን ፖሊስ ስለያዘው ምንም ማለት አልችልም፤›› የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

በዝርፊያው ተጠርጥረው በጃንሜዳ አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ስለታሰሩት ተጠርጣሪዎችና ፖሊስ ስለደረሰበት የምርመራ ውጤት ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አለመሳካቱም ተገልጿል፡፡

No comments:

Post a Comment