Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Friday, August 31, 2012

አዲስ አበባ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በከፍተኛ የጸጥታ ቁጥጥር ስር ትገኛለች ተባለ::

ኢሳት ዜና:- ዘጋቢያችን እንደገለጠው በዛሬው እለት እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፌደራል ፖሊስ አባላት በከተማዋ የተለያዩ ክፍሎች ተሰማርተው የጸጥታ ስራ እየሰሩ ነው።

የጸጥታ ቁጥጥሩ እንዲጠናከር የሆነበትን ትክክለኛ ምክንያት ለማወቅ ባይቻልም በአንድ በኩል የሙስሊሙ ማህበረሰብ በነገው እለት ተቃውመ ያነሳል በሚል ፍርሀት ወይም በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት በመስቀል አደባባይ የሚካሄደው የአቶ መለስ ዜናዊ ልዩ የሽኝት መርሀግብር እንዳይደናቀፍ ለማድረግ ታስቦ ሊሆን እንደሚችል ግምቱን አስፍሯል።


ሙስሊሙ ማህበረሰብ በነገው እለት ተቃውሞውን ይቀጥል አይቀጥል እስካሁን የታወቀ ነገር የለም። ይሁን እንጅ የአቶ መለስ ዜናዊ ግብአተ ምድር እንደተፈጸመ ተቃውሞው እንደሚቀጥል የኢሳት የመረጃ ምንጮች ገልጠዋል።

No comments:

Post a Comment