Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Friday, August 31, 2012

ህዝቡ በአቶ መለስ ዜናዊ የተንዛዛ የለቅሶ ስርአት ተቃውሞውን እየገለጠ ነው::

ኢሳት ዜና:- የኢሳት ዘጋቢዎች ያነጋገሩዋቸው የህብረተስብ ክፍሎች እንደገለጡት የአቶ መለስ ዜናዊ የተንዛዛ የለቅሶ ስርአት በህይወታቸው ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እያመጣ ነው።

አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ በኢግዚቢሽን ማእከል ውስጥ በሚካሄደው ባዛር  ባለፈው ሳምንት በ20 ሺ ብር የንግድ ቦታ የገዛ ሰው ለኢሳት እንደተናገረው ፣ የአቶ መለስ ዜናዊን እረፍት ተከትሎ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ሆነ የራዲዮ ጣቢያዎች ማስታወቂያዎችን ማስተላለፍ በማቆማቸው፣ የእርሳቸውና በውስጡ ከፍተኛ ገንዘብ በማፍሰስ ቦታ የገዙ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ነጋዴዎች ለከፍተኛ ኪሳራ ተዳርገዋል።


የህዝቡን ሀዘን የሚያደናቅፍ ምንም አይነት ስራ መስራት አይቻልም የሚለው የመንግስት መመሪያ ፣ ከውጭ አገር አላቂ እና ፍጆታ እቃዎችን ያመጡ አስመጪዎችንም ክፉኛ መጉዳቱን ነው ነጋዴዎች የሚናገሩት። በፍጥነት ተሽጠው ከባንክ የተበደሩትን ገንዘብ መመለስ የነበረባቸው ነጋዴዎች ማስታዎቂያዎችን ለማስተላለፍ ባለመቻላቸው እቃዎቻቸውን ለመሸጥ አለመቻላቸውን በምሬት ገልጠዋል።

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ራዲዮ ከሀዘን ውጭ የሆኑ ማስታወቂያዎችን ለማቅረብ ባለመቻሉም ድርጅቱ ለኪሳራ መዳረጉን በድርጅቱ ውስጥ የሚሰሩ ጋዜጠኞች ለኢሳት ተናግረዋል። ጋዜጠኞቹ እንዳሉት ነጋዴዎችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች ቁጣቸውን እየገለጡ ነው።

በሌላ በኩል ደግሞ በአማራ ክልል አስለቃሾች እና ፉከራና ሽለላ የሚያሰሙ ሰዎች በቀን 500 ብር እየተከፈላቸው የለቅሶ ስርአት እያደረጉ ነው። የኢህአዴግ ካድሬዎችም ህዝቡን ያለቀሰና ያላላቀሰ በማለት እየለዩ እንደሚገኙ ኢሳት ያነጋገርናቸው ሰዎች ገልጠዋል።

ዩኒቨርስቲዎችም በአቶ መለስ ዜናዊ ምክንያት የምረቃ ስነስርአታቸውን አራዝመዋል፡፡ የመቀሌ እና ዩኒቲ ዩኒቨርስቲዎች የምረቃ ስነ ስርዓታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀብር እስኪፈፀም ላልተወሰነ ጊዜ አራዝመውታል::

No comments:

Post a Comment