Welcome!

"If you are neutral 0n the situations of injustice, You have choosen the side of oppressors." -Desmond tutu

Wednesday, July 11, 2012

የህዝበ-ሙስሊም የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል ከሆቴላቸው በፖሊስ ታፍነው ተወሰዱ

ኢሳት ዜና:- ሐምሌ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
በኮምቦልቻ ከተማ በዛሬዉ እለት በተካሄደዉ ደማቅ የአንድነትና የሰደቃ ፕሮግራም ላይ ተካፍለዉ የነበሩት የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆኑት ሼህ መከተ ሞሄ በፖሊስ ታፍነዉ መታሰራቸዉን በስፍራው የሚገኘው የኢሳት ወኪል ዘግቧል።

ሼህ መኸተ ሞሄ የታሰሩት ፕሮግራሙን ጨርሰዉ ወደ ማረፊያ ሆቴላቸዉ ከገቡ ቡሁዋላ በበርካታ ፖሊሶች ታፍነው ነው።

ከሸህ መከተ በተጨማሪ በኮምቦልቻ ፕሮግራም ላይ ከተካፈሉት መካከል፤  ታዎቂዉ “ዳኢ” እና የሙስሊሙ ማህበረሰብ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆነዉ ኡስታዝ ያሲን ኑሩም በፖሊሶች እየተፈለገ መሆኑን ወኪላችን ያጠናቀረው ዘገባ ያመለክታል።

በአሁኑ ጊዜ  የአካባቢው ፖሊስ ኡስታዝ ያሲን ኑሩን ለማሰር ከተማዋን እያሰሰ መሆኑን ምንጮች ገልፀዋል!!
Source: Ethsat news :የህዝበ-ሙስሊም የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል ከሆቴላቸው በፖሊስ ታፍነው ተወሰዱ

No comments:

Post a Comment