Monday, December 24, 2012

የኢትዮ ቴሌኮምና የፍራንስ ቴሌኮም ኮንትራት ትላንት ተጠናቀቀ

የቀድሞውን የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ማኔጅመንት በመረከብ ከሁለት ዓመታት ከስድስት ወራት በፊት ኢትዮ ቴሌኮም ብሎ ሥራውን የጀመረው ፍራንስ ቴሌኮም፤ ኮንትራቱን ከትናንት በስቲያ አጠናቀቀ፡፡ ኩባንያው ኮንትራቱን በማጠናቀቁ ቢሰናበትም አራት የሥራ ኃላፊዎች ግን በኮንትራት እንዲቀጥሉ መደረጉን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

፮ኛውን ፓትርያርክ የሚያስመርጥ ኰሚቴ በመሰየሙ ዜና ላይ ብፁዓን አባቶች እየተናገሩ ነው

ኢትዮጵያ የሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ ረቡዕ ታኅሣሥ 10 ቀን 2005 ዓም ፮ኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ፓትርያርክ የሚያስመርጥ ኰሚቴ መሰየሙን ከአዲስ አበባ ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።